የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 9/00 ገጽ 1
  • የሰዎች ሕይወት አደጋ ተጋርጦበታል!

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የሰዎች ሕይወት አደጋ ተጋርጦበታል!
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2000
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ልናውጀው የሚገባ መልእክት
    በቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት ከሚሰጠው ሥልጠና ተጠቀም
  • መስበካችሁን ቀጥሉ!
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2000
  • አገልግሎትህን በተሟላ ሁኔታ እየፈጸምክ ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2019
  • ‘በጌታ የተቀበልከውን አገልግሎት ለመፈጸም ትኩረት ስጥ’
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2008
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2000
km 9/00 ገጽ 1

የሰዎች ሕይወት አደጋ ተጋርጦበታል!

1 የይሖዋ ፈቃድ ‘ሰዎች ሁሉ መዳንን እንዲያገኙ’ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ይናገራል። ይሁን እንጂ በቢልዮን የሚቆጠሩት የምድር ነዋሪዎች የወደፊት ዕጣ የተመካው ለይሖዋ አምላክና በኢየሱስ ክርስቶስ ለሚመራው መንግሥት ባላቸው ዝንባሌ ላይ እንደሆነ የታወቀ ነው። ተገቢውን ዝንባሌ መያዝ የሚቻለው ‘ትክክለኛ የእውነት እውቀት’ በማግኘት ብቻ ነው። (1 ጢ⁠ሞ. 2:​3, 4) ለአምላክ አዲስ የጽድቅ ዓለም መንገድ ለማዘጋጀት በቅርቡ ክፋት ከምድር ላይ የሚወገድበትን ጊዜ በጉጉት እየተጠባበቅን በጣም አስፈላጊ የሆነውን ሕይወት አድን ሥራ እንድናከናውን ተልዕኮ ተሰጥቶናል።​—⁠ማቴ. 24:​14፤ 28:​19, 20፤ ሮሜ 10:​13-15

2 ይህን ያህል አጣዳፊ የሆነው ለምንድን ነው? ኢየሱስ “ከዓለም መጀመሪያ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ያልሆነ . . . ታላቅ መከራ” እንደሚመጣ አስጠንቅቋል። (ማቴ. 24:​21) ይህ ታላቅ መከራ የሚደመደመው በአርማጌዶን ነው። (ራእይ 16:​16) የማያምኑ ዘመዶቻችንን፣ ጎረቤቶቻችንን፣ የሥራ ባልደረቦቻችንን፣ የትምህርት ቤት ጓደኞቻችንንና ሌሎች የምናውቃቸውን ሰዎች ጨምሮ በጣም ብዙ ሰዎች ለምሥራቹ ጥሩ ምላሽ ካልሰጡ በስተቀር ጥፋት ተደቅኖባቸዋል። ሆኖም ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ቤዛ አድርጎ በመስጠት ለመላው የሰው ዘር ዓለም ያለውን ፍቅር የገለጸውን የአምላክን ምሳሌ በመኮረጅ ምሥራቹን ‘ለሰዎች ሁሉ’ ማዳረስ ይኖርብናል። (ዮሐ. 3:​16) ሁሉም፣ አምላክ ለደህንነት ወዳዘጋጀው ስፍራ እንዲሸሹ ለመጋበዝ በቅንዓት መንቀሳቀስ ይገባናል። በስብከቱ ሥራ ሙሉ በሙሉ በመካፈል የደም ዕዳ እንዳይኖርብን ማድረግ እንችላለን።​—⁠ሕዝ. 33:​1-7፤ 1 ቆ⁠ሮ. 9:​16

3 ዓላማችን ምንድን ነው? የስብከቱ ሥራ አስፈላጊነት በአምላክ ቃል ውስጥ ጠበቅ ተደርጎ ተገልጿል። ሐዋርያው ጳውሎስ እንደገለጸው ከአምላክ መንገድ ጋር ተስማምተን እንድንኖር ‘የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናል።’ (2 ቆ⁠ሮ. 5:​14) በተጨማሪም መጠበቂያ ግንብ ብዙውን ጊዜ የመስበክ ግዴታችንን ጠበቅ አድርጎ ይገልጻል። የመንግሥት አገልግሎታችን የስብከቱን ሥራ እንዴት እንደምናከናውን የሚጠቁም መመሪያ በየጊዜው ይዞ ይወጣል። ሽማግሌዎች ሥራውን ያደራጃሉ እንዲሁም እንድንካፈል ማበረታቻ ይሰጡናል። ሌሎች አስፋፊዎችም አብረናቸው እንድናገለግል ይጋብዙናል። አቀራረባችንን ስለመዘጋጀት፣ መጽሔቶችንና ሌሎች ጽሑፎችን ስለማበርከት፣ ተመላልሶ መጠየቆችን ስለማድረግ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶችን ስለመምራት እንዲሁም በእያንዳንዱ አጋጣሚ ምሥክርነት ስለመስጠት ብዙ ተመክረናል። ይህ ሁሉ ሕይወትን የማዳን ዓላማችንን ከግብ ለማድረስ ይረዳናል።​—⁠1 ቆ⁠ሮ. 9:​22, 23፤ ኤፌ. 1:​13

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ