የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ijwyp ርዕስ 110
  • ልጠመቅ?—ክፍል 2፦ ለጥምቀት መዘጋጀት

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ልጠመቅ?—ክፍል 2፦ ለጥምቀት መዘጋጀት
  • የወጣቶች ጥያቄ
  • ንዑስ ርዕሶች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ምን ያህል እውቀት ሊኖረኝ ይገባል?
  • ምን ዓይነት ምግባር ሊኖረኝ ይገባል?
  • ወጣቶች—ለጥምቀት መዘጋጀት የምትችሉት እንዴት ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2016
  • መጠመቅ ይኖርብኝ ይሆን?
    ወጣቶች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎችና ተግባራዊ መሆን የሚችሉ መልሶች፣ ጥራዝ 2
  • ለመጠመቅ ዝግጁ ነህ?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
  • ጥምቀት—ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ግብ!
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
ለተጨማሪ መረጃ
የወጣቶች ጥያቄ
ijwyp ርዕስ 110
አንዲት ወጣት መጽሐፍ ቅዱስንና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጽሑፎችን ተጠቅማ ስለ ጥምቀት ምርምር ስታደርግ።

የወጣቶች ጥያቄ

ልጠመቅ?—ክፍል 2፦ ለጥምቀት መዘጋጀት

የመጽሐፍ ቅዱስን መሥፈርቶች እየተከተልክ እንዲሁም ከአምላክ ጋር ወዳጅነት ለመመሥረት እየጣርክ ከሆነ ስለ ጥምቀት ማሰብህ አይቀርም። ታዲያ ይህን እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆንህን ማወቅ የምትችለው እንዴት ነው?a

በዚህ ርዕስ ውስጥ

  • ምን ያህል እውቀት ሊኖረኝ ይገባል?

  • ምን ዓይነት ምግባር ሊኖረኝ ይገባል?

  • እኩዮችህ ምን ይላሉ?

ምን ያህል እውቀት ሊኖረኝ ይገባል?

ለጥምቀት መዘጋጀት ሲባል በትምህርት ቤት ፈተና ለማለፍ እንደሚደረገው አንዳንድ መረጃዎችን መሸምደድ ማለት አይደለም። ከዚህ ይልቅ ‘የማሰብ ችሎታህን በመጠቀም’ መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረው ነገር እውነት ስለመሆኑ ያለህን እምነት ማጠናከር ይኖርብሃል። (ሮም 12:1) ለምሳሌ ያህል፦

  • አምላክ መኖሩንና ልታመልከው እንደሚገባ ታምናለህ?

    መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? “ወደ አምላክ የሚቀርብ ሁሉ እሱ መኖሩንና ከልብ ለሚፈልጉትም ወሮታ ከፋይ መሆኑን ማመን ይኖርበታል።”—ዕብራውያን 11:6

    ራስህን እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦ ‘በአምላክ የማምነው ለምንድን ነው?’ (ዕብራውያን 3:4) ‘ላመልከው የሚገባውስ ለምንድን ነው?’—ራእይ 4:11

    እገዛ ትፈልጋለህ? “ፍጥረት ወይስ ዝግመተ ለውጥ?—ክፍል 1፦ አምላክ መኖሩን እንዳምን ያደረገኝ ምንድን ነው?” የሚለውን ርዕስ ተመልከት።

  • መጽሐፍ ቅዱስ የአምላክ ቃል መሆኑን ታምናለህ?

    መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? “ቅዱሳን መጻሕፍት ሁሉ በአምላክ መንፈስ መሪነት የተጻፉ ናቸው፤ እንዲሁም ለማስተማር፣ ለመውቀስ፣ ነገሮችን ለማቅናትና በጽድቅ ለመገሠጽ ይጠቅማሉ።”—2 ጢሞቴዎስ 3:16

    ራስህን እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦ ‘መጽሐፍ ቅዱስ የሰዎችን ሐሳብ የያዘ መጽሐፍ እንዳልሆነ የማምነው ለምንድን ነው?’—ኢሳይያስ 46:10፤ 1 ተሰሎንቄ 2:13

    እገዛ ትፈልጋለህ? “መጽሐፍ ቅዱስ ሊጠቅመኝ የሚችለው እንዴት ነው?—ክፍል 1፦ መጽሐፍ ቅዱስን መመርመር” የሚለውን ርዕስ ተመልከት።

  • ይሖዋ ፈቃዱን ለመፈጸም በክርስቲያን ጉባኤ እንደሚጠቀም ታምናለህ?

    መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? “[ለአምላክ] በጉባኤው አማካኝነትና በክርስቶስ ኢየሱስ አማካኝነት በትውልዶች ሁሉ ለዘላለም ክብር ይሁን።”—ኤፌሶን 3:21

    ራስህን እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦ ‘በክርስቲያናዊ ስብሰባዎች ላይ የማገኘው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ከሰዎች ሳይሆን ከይሖዋ የመጣ እንደሆነ ይሰማኛል?’ (ማቴዎስ 24:45) ‘ወላጆቼ በማይችሉበት ጊዜም በስብሰባዎች ላይ እገኛለሁ? (ወላጆችህ የሚፈቅዱልህ ከሆነ ማለት ነው።)’—ዕብራውያን 10:24, 25

    እገዛ ትፈልጋለህ? “በስብሰባ አዳራሽ በሚደረጉ ስብሰባዎች ላይ መገኘት ያለብኝ ለምንድን ነው?” የሚለውን ርዕስ ተመልከት።

ምን ዓይነት ምግባር ሊኖረኝ ይገባል?

መጠመቅ እንድትችል ፍጹም መሆን አይጠበቅብህም። ሆኖም ‘ክፉ ከሆነ ነገር መራቅና መልካም የሆነውን ማድረግ’ ከልብህ እንደምትፈልግ በምግባርህ ማሳየት ይኖርብሃል። (መዝሙር 34:14) ለምሳሌ ያህል፦

  • አኗኗርህ ከይሖዋ መሥፈርቶች ጋር የሚስማማ ነው?

    መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? “ጥሩ ሕሊና ይኑራችሁ።”—1 ጴጥሮስ 3:16

    ራስህን እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦ ‘“ትክክልና ስህተት የሆነውን ነገር መለየት” እንድችል የማስተዋል ችሎታዬን እንዳሠለጠንኩ ያሳየሁት እንዴት ነው?’ (ዕብራውያን 5:14) ‘የእኩዮቼን መጥፎ ተጽዕኖ የተቋቋምኩባቸውን ጊዜያት መጥቀስ እችላለሁ? ጓደኛ የማደርገው ትክክል የሆነውን ነገር እንዳደርግ የሚያበረታቱኝን ሰዎች ነው?’—ምሳሌ 13:20

    እገዛ ትፈልጋለህ? “ሕሊናዬን ማሠልጠን የምችለው እንዴት ነው?” የሚለውን ርዕስ ተመልከት።

  • ለድርጊትህ ኃላፊነት ትወስዳለህ?

    መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? “እያንዳንዳችን ስለ ራሳችን ለአምላክ መልስ እንሰጣለን።”—ሮም 14:12

    ራስህን እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦ ‘ለራሴም ሆነ ለሌሎች ሐቀኛ ነኝ?’ (ዕብራውያን 13:18) ‘ስህተቴን አምናለሁ? ወይስ ስህተቴን ለመሸፋፈን ወይም በሌሎች ለማሳበብ እሞክራለሁ?’—ምሳሌ 28:13

    እገዛ ትፈልጋለህ? “ስህተት ስሠራ ምን ማድረግ ይኖርብኛል?” የሚለውን ርዕስ ተመልከት።

  • ከይሖዋ ጋር ያለህን ወዳጅነት ለማጠናከር ጥረት እያደረግክ ነው?

    መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? “ወደ አምላክ ቅረቡ፤ እሱም ወደ እናንተ ይቀርባል።”—ያዕቆብ 4:8

    ራስህን እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦ ‘ወደ ይሖዋ ለመቅረብ ስል የትኞቹን እርምጃዎች እየወሰድኩ ነው?’ ለምሳሌ ‘መጽሐፍ ቅዱስን አዘውትሬ አነብባለሁ?’ (መዝሙር 1:1, 2) ‘አዘውትሬ እጸልያለሁ?’ (1 ተሰሎንቄ 5:17) ‘በደፈናው ከመጸለይ ባለፈ ዝርዝር ጉዳዮችን እጠቅሳለሁ? ጓደኞቼ የይሖዋ ወዳጆች ናቸው?’—መዝሙር 15:1, 4

    እገዛ ትፈልጋለህ? “መጽሐፍ ቅዱስ ሊጠቅመኝ የሚችለው እንዴት ነው?—ክፍል 2፦ የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብህን አስደሳች ማድረግ” እና “መጸለይ ጥቅም አለው?” የሚሉትን ርዕሶች ተመልከት።

ጠቃሚ ምክር፦ ለጥምቀት ለመዘጋጀት እንዲረዳህ ወጣቶች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎችና ተግባራዊ መሆን የሚችሉ መልሶች፣ ጥራዝ 2 የተባለውን መጽሐፍ ምዕራፍ 37⁠ን አንብብ። በተለይ በገጽ 308 እና 309 ላይ ለሚገኘው የመልመጃ ሣጥን ትኩረት ስጠው።

a ራስን ለአምላክ መወሰንና መጠመቅ ስላለው ትርጉም እንዲሁም አስፈላጊነት የሚናገረውን “ልጠመቅ?—ክፍል 1” የሚለውን ርዕስ አንብብ።

እኩዮችህ ምን ይላሉ?

ጋብሪዬላ።

“የወጣቶች ጥያቄ በሚለው መጽሐፍ ላይ የሚገኘው ስለ ጥምቀት የሚናገረው የመልመጃ ሣጥን ከመጠመቄ በፊት በየትኞቹ አቅጣጫዎች ማሻሻያ ማድረግ እንዳለብኝ እንዳስተውል ረድቶኛል። በተጨማሪም ከተጠመቅኩ በኋላ ልደርስባቸው የምፈልጋቸውን ግቦች እንዳወጣ ረድቶኛል። ራስን ለይሖዋ መወሰን ትልቅ ኃላፊነት ያስከትላል፤ ሆኖም አንድ ሰው ሊያገኘው የሚችለው ከሁሉ የላቀ መብት ነው።”—ጋብሪዬላ

ካሌብ።

“መጽሐፍ ቅዱስ፣ ጢሞቴዎስ ‘በተማርካቸውና አምነህ በተቀበልካቸው ነገሮች ጸንተህ ኑር’ የሚል ምክር እንደተሰጠው ይናገራል።” (2 ጢሞቴዎስ 3:14) “የአምላክ ቃል የሚያስተምረው ነገር እውነት መሆኑን ሙሉ በሙሉ መተማመን እንድትችሉ ጊዜ ወስዳችሁ መጽሐፍ ቅዱስን አጥኑ። ራሳችሁን የምትወስኑት ለሰዎች ሳይሆን ለይሖዋ ነው፤ ስለዚህ ስለ ጥምቀት ስታስቡ በዋነኝነት ሊያሳስባችሁ የሚገባው ‘ይሖዋ ምን ይሰማዋል’ የሚለው ነው።”—ካሌብ

ክለሳ፦ ለጥምቀት መዘጋጀት የምችለው እንዴት ነው?

እምነትህን ፈትሽ። አምላክ መኖሩን ታምናለህ? ልታመልከው እንደሚገባስ ታምናለህ? መጽሐፍ ቅዱስ የአምላክ ቃል መሆኑን ታምናለህ? ይሖዋ ፈቃዱን ለመፈጸም በድርጅቱ እንደሚጠቀም ታምናለህ?

ምግባርህን ፈትሽ። አኗኗርህ ከይሖዋ መሥፈርቶች ጋር የሚስማማ ነው? ለድርጊትህ ኃላፊነት ትወስዳለህ? ከይሖዋ ጋር ያለህን ወዳጅነት ለማጠናከር ጥረት እያደረግክ ነው?

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ