የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ijwbq ርዕስ 49
  • ዲያብሎስ የሚኖረው የት ነው?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ዲያብሎስ የሚኖረው የት ነው?
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • ንዑስ ርዕሶች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?
  • የዘላለም ሕይወት ጠላት
    በምድር ላይ በገነት ለዘላለም መኖር ትችላለህ
  • ሰይጣን
    ንቁ!—2013
  • ኢየሱስ እንዳደረገው “ዲያብሎስን ተቃወሙት”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2008
  • በመንፈሳዊው ዓለም ውስጥ ያሉ ገዥዎች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1995
ለተጨማሪ መረጃ
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
ijwbq ርዕስ 49

ዲያብሎስ የሚኖረው የት ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?

ዲያብሎስ መንፈሳዊ ፍጡር እንደመሆኑ መጠን የሚኖረው በዓይን በማይታይ መንፈሳዊ ዓለም ውስጥ ነው። ያም ቢሆን ይህ ቦታ፣ በዚህ ርዕስ ላይ ባለው ሥዕል ላይ እንደሚታየው ያለ ይኸውም ሰይጣን ክፉዎችን የሚያሠቃይበት እሳታማ ሲኦል አይደለም።

‘በሰማይ ጦርነት ተነሳ’

ለተወሰነ ጊዜ ሰይጣን ዲያብሎስ በመንፈሳዊው ዓለም ውስጥ እንደፈለገ ይንቀሳቀስ ነበር፤ ለምሳሌ ከታማኝ መላእክት ጋር በአምላክ ፊት መቆም ይችል ነበር። (ኢዮብ 1:6) ይሁን እንጂ መጽሐፍ ቅዱስ ‘በሰማይ ጦርነት እንደሚነሳ’ እንዲሁም ሰይጣን ከሰማይ “ወደ ምድር [እንደሚወረወር]” ትንቢት ተናግሯል። (ራእይ 12:7-9) የመጽሐፍ ቅዱስ የዘመን አቆጣጠርም ሆነ በዓለም ውስጥ የተከናወኑት ነገሮች ይህ ጦርነት እንደተካሄደ ያረጋግጣሉ። በአሁኑ ጊዜ ዲያብሎስ በምድር አካባቢ ብቻ ተወስኖ እንዲኖር ተደርጓል።

ታዲያ ይህ ማለት ዲያብሎስ የሚኖረው በምድር ላይ ባለ አንድ የተወሰነ ቦታ ላይ ነው? ለምሳሌ ያህል፣ ጴርጋሞን የተባለው ጥንታዊ ከተማ “የሰይጣን ዙፋን [ያለበት]” እንዲሁም ‘ሰይጣን ያለበት’ ከተማ እንደሆነ ተገልጿል። (ራእይ 2:13) በእርግጥ፣ እነዚህ አገላለጾች በዚህ ከተማ ውስጥ የሰይጣን አምልኮ እንደተስፋፋ የሚያሳዩ መሆን አለባቸው። መጽሐፍ ቅዱስ፣ ዲያብሎስ “የዓለምን መንግሥታት ሁሉ” እንደሚገዛ ይናገራል፤ ከዚህ አንጻር ዲያብሎስ የሚኖረው በምድር ላይ ባለ አንድ የተወሰነ ቦታ ላይ ሳይሆን እንቅስቃሴው በምድር አካባቢ ብቻ እንደተገደበ መደምደም እንችላለን።​—ሉቃስ 4:5, 6

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ