የግርጌ ማስታወሻ
a ይሖዋ በቀይ ባሕር የፈጸመውን ተአምር ያዩት አብዛኞቹ እስራኤላውያን ወደ ተስፋይቱ ምድር አልገቡም። (ዘኁ. 14:22, 23) ይሖዋ 20 ዓመትና ከዚያ በላይ ሆኗቸው የተመዘገቡት እስራኤላውያን በምድረ በዳ እንደሚሞቱ ተናግሮ ነበር። (ዘኁ. 14:29) ሆኖም ኢያሱ፣ ካሌብ፣ ከወጣቱ ትውልድ መካከል ብዙዎቹ እንዲሁም አብዛኞቹ ሌዋውያን ይሖዋ ቃል በገባው መሠረት ዮርዳኖስ ወንዝን ተሻግረው ወደ ከነአን ምድር ገብተዋል።—ዘዳ. 1:24-40