-
ወላጆች ያሳዩት እምነት ወሮታ አስገኘመጠበቂያ ግንብ—1997 | ግንቦት 1
-
-
ሚርያም የምትባለው የዮኬቤድ ልጅ የሚፈጸመውን ነገር ለማየት በአቅራቢያው ቆማ ነበር። ከዚያ የፈርዖን ልጅ ገላዋን ለመታጠብ ወደ አባይ ወንዝ መጣች።a ምናልባት ዮኬቤድ ልዕልቷ በዚህ አካባቢ እንደምታዘወትር ስለምታውቅ ቅርጫቱን በቀላሉ መታየት በሚችልበት ቦታ አስቀምጣው ይሆናል። ያም ሆነ ይህ የፈርዖን ልጅ በመቃው መካከል ተመቻችቶ የተቀመጠውን ቅርጫት ተመለከተችና አገልጋይዋን ጠርታ አስመጣችው። በቅርጫቱ ውስጥ አንድ የሚያለቅስ ልጅ ስታይ አዘነችለት። የዕብራውያን ልጅ መሆኑን ተገነዘበች። ሆኖም ይህን ውብ ሕፃን እንዴት ልታስገድለው ትችላለች? ከሰብዓዊ ደግነት በተጨማሪ በወቅቱ የነበረው አንድ ሰው ወደ ሰማይ ለመግባት በሕይወቱ የደግነት ተግባር መፈጸም አለበት የሚለው የግብፃውያን እምነት በፈርዖን ልጅ ላይ ተጽዕኖ አሳድሮ ሊሆን ይችላል።b— ዘጸአት 2:5, 6
-
-
ወላጆች ያሳዩት እምነት ወሮታ አስገኘመጠበቂያ ግንብ—1997 | ግንቦት 1
-
-
a ግብፃውያን የመራባት አምላክ ነው በማለት የአባይ ወንዝን ያመልኩ ነበር። ውኃው ፍሬያማ የሚያደርግ እንዲያውም ዕድሜ የሚያራዝም የመፈወስ ኃይል አለው ብለው ያምኑ ነበር።
-