-
“ለይሖዋ ዘምሩ”!በእምነታቸው ምሰሏቸው
-
-
ሚርያምስ ተደስታ ይሆን? መጀመሪያ ላይ ተደስታ ሊሆን ይችላል። ከጊዜ በኋላ ግን በኩራት የተሸነፈች ይመስላል። ሚርያም ሲፓራ በብሔሩ ውስጥ ከፍተኛ ታዋቂነት በማግኘት የእሷን ቦታ ልትወስድ እንደምትችል በማሰብ ሰግታ ሊሆን ይችላል። ያም ሆነ ይህ ሚርያምና አሮን አሉታዊ ነገር መናገር ጀመሩ። እንዲህ ያለው ንግግር ደግሞ ተባብሶ መራራና ጎጂ መሆኑ እንደማይቀር የታወቀ ነው። መጀመሪያ ላይ ወሬው ያጠነጠነው በሲፓራ ዙሪያ ነበር፤ ሲፓራ ኩሻዊት እንጂ እስራኤላዊት እንዳልሆነች በመናገር አጉረመረሙ።a በጊዜ ሂደት ግን ሁኔታው ተባብሶ በሙሴ ላይም ማጉረምረም ጀመሩ። ሚርያምና አሮን “ለመሆኑ ይሖዋ የሚናገረው በሙሴ አማካኝነት ብቻ ነው? በእኛስ በኩል አልተናገረም?” ይሉ ነበር።—ዘኁልቁ 12:1, 2
-
-
“ለይሖዋ ዘምሩ”!በእምነታቸው ምሰሏቸው
-
-
a ከሲፓራ ጋር በተያያዘ “ኩሻዊት” የሚለው ቃል የተሠራበት ኢትዮጵያዊት መሆኗን ለማመልከት ሳይሆን እንደ ሌሎቹ ምድያማውያን ከዓረብ አገር የመጣች መሆኑን ለማመልከት ነው።
-