-
ትዕቢት ውርደትን ያስከትላልመጠበቂያ ግንብ—2000 | ነሐሴ 1
-
-
ቆሬ—ቅናት ያደረበት ዓመፀኛ
4. (ሀ) ቆሬ ማን ነው? በየትኛው ታሪካዊ ክንውን ውስጥ ተካፋይ ሳይሆን አይቀርም? (ለ) ቆሬ ወደኋላ ላይ ምን መጥፎ ድርጊት ፈጸመ?
4 ቆሬ ከቀዓት ወገን የሆነ ሌዋዊ ሲሆን የሙሴና የአሮን የአጎት ልጅ ነው። ለአሥርተ ዓመታት ይሖዋን በታማኝነት ሲያገለግል እንደነበረ ግልጽ ነው። ቆሬ ተዓምራዊ በሆነ መንገድ ቀይ ባሕርን በሕይወት የመሻገር መብት ካገኙት ሰዎች መካከል አንዱ ከመሆኑም በላይ በሲና ተራራ በጥጃ አምልኮ በተካፈሉ እስራኤላውያን ላይ የይሖዋን ፍርድ ካስፈጸሙት ሰዎች መካከል አንዱ ሳይሆን አይቀርም። (ዘጸአት 32:26) ዳሩ ምን ያደርጋል በመጨረሻ የሮቤልን ልጆች ዳታንን፣ አቤሮንን እና አንን ጨምሮ 250 የእስራኤል አለቆች በሙሴና በአሮን ላይ እንዲያምፁ በማድረግ ረገድ ቀንደኛ የዓመፁ መሪ ሆነ።a “ማኅበሩ ሁሉ እያንዳንዳቸው ቅዱሳን ናቸውና፣ እግዚአብሔርም በመካከላቸው ነውና እናንተ እጅግ አብዝታችኋል፤ በእግዚአብሔርም ጉባኤ ላይ ለምን ትታበያላችሁ?” በማለት በሙሴና በአሮን ላይ ተናገሩ።—ዘኁልቁ 16:1-3
-
-
ትዕቢት ውርደትን ያስከትላልመጠበቂያ ግንብ—2000 | ነሐሴ 1
-
-
a ሮቤል የያዕቆብ የበኩር ልጅ እንደመሆኑ የእርሱ ዘሮች ከቆሬ ጋር አብረው ያመፁት ሌዋዊው ሙሴ በእነርሱ ላይ ያለውን የማስተዳደር ሥልጣን ለመቀበል ፈቃደኞች ስላልነበሩ ሊሆን ይችላል።
-