የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “ወደምትሄጂበት እሄዳለሁ”
    በእምነታቸው ምሰሏቸው
    • 23. ሩት ስለ ምን ነገር ማሰብ ጀመረች? የሙሴ ሕግ ድሆች ከየትኛው ዝግጅት እንዲጠቀሙ ይፈቅድ ነበር? (የግርጌ ማስታወሻውንም ተመልከት።)

      23 ሁለቱ ሴቶች በቤተልሔም ኑሯቸውን ሲመሠርቱ ሩት ራሷንም ሆነ ኑኃሚንን እንዴት በተሻለ ሁኔታ ማስተዳደር እንደምትችል ማሰብ ጀመረች። ይሖዋ በእስራኤል ለሚኖሩ ሕዝቦቹ በሰጠው ሕግ ውስጥ ድሆች የሚያስፈልጋቸውን ነገር እንዲያገኙ የሚያስችል ፍቅራዊ ዝግጅት እንዳለ አወቀች። አዝመራ በሚሰበሰብበት ወቅት ድሆች ወደ ሌሎች ማሳ በመሄድ አጫጆቹን እየተከተሉ ከኋላ የወዳደቀውንና ከማሳው ዳርና ዳር የበቀለውን እንዲቃርሙ ይፈቀድላቸው ነበር።b—ዘሌ. 19:9, 10፤ ዘዳ. 24:19-21

      24, 25. ሩት በአጋጣሚ ወደ ቦዔዝ እርሻ በሄደች ጊዜ ምን አደረገች? የመቃረሙ ሥራስ ምን ይመስል ነበር?

      24 ጊዜው ገብስ የሚታጨድበት ወቅት ሲሆን በዘመናችን የቀን አቆጣጠር መሠረት ወሩ ሚያዝያ ሳይሆን አይቀርም፤ ሩት በሕጉ ውስጥ በሰፈረው ዝግጅት መሠረት በማሳው ላይ እንድትቃርም የሚፈቅድላት ሰው ለማግኘት ወደ እርሻ ቦታዎች ሄደች። እንዳጋጣሚ ሆኖ የሄደችበት እርሻ ባለቤት ቦዔዝ የተባለ ሀብታም ባለርስት ሲሆን እሱም የኑኃሚን ባል የሆነው የሟቹ የአቤሜሌክ ዘመድ ነበር። ምንም እንኳ ሩት በሕጉ መሠረት የመቃረም መብት ቢኖራትም ፈቃድ ሳትጠይቅ ሥራዋን አልጀመረችም፤ ከዚህ ይልቅ ወደ አጫጆቹ አለቃ ቀርባ መቃረም ትችል እንደሆነ ጠየቀችው። እሱም እንድትቃርም ፈቀደላት፤ በመሆኑም ሩት ወዲያውኑ ሥራዋን ጀመረች።—ሩት 1:22 እስከ 2:3, 7

  • “ወደምትሄጂበት እሄዳለሁ”
    በእምነታቸው ምሰሏቸው
    • b በዚህ ሕግ ውስጥ የተካተተው አስደናቂ ዝግጅት ሩት በትውልድ አገሯ ከምታውቀው ፈጽሞ የተለየ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። በዚያ ዘመን በመካከለኛው ምሥራቅ መበለቶች በደል ይደርስባቸው ነበር። አንድ የማመሳከሪያ ጽሑፍ እንዲህ ይላል፦ “አንዲት ሴት ባሏ ከሞተ በኋላ በአብዛኛው ደጋፊና ጧሪ የሚሆኗት ወንዶች ልጆቿ ነበሩ፤ ወንዶች ልጆች ከሌሏት ግን ያላት አማራጭ ራሷን ለባርነት መሸጥ፣ ዝሙት አዳሪ መሆን አለዚያም መሞት ነበር።”

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ