-
“ስእለትህን ፈጽም”መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2017 | ሚያዝያ
-
-
7. (ሀ) ሐና ለአምላክ ምን ተሳለች? ይህን ያደረገችው ለምንድን ነው? ውጤቱስ ምን ሆነ? (ለ) የሐና ስእለት በሳሙኤል ሕይወት ላይ ምን ለውጥ አስከትሏል? (የግርጌ ማስታወሻውን ተመልከት።)
7 ሐናም ለይሖዋ የተሳለችውን ስእለት በታማኝነት ፈጽማለች። ሐና መሃን በመሆኗ ምክንያት ውስጧ በብሶትና በጭንቀት ተሞልቶ ነበር፤ በዚያ ላይ ደግሞ ጣውንቷ ዘወትር ትሳለቅባት ነበር። (1 ሳሙ. 1:4-7, 10, 16) በዚህ የተነሳ ለአምላክ የልቧን አውጥታ በማፍሰስ እንዲህ ስትል ተሳለች፦ “የሠራዊት ጌታ ይሖዋ ሆይ፣ አገልጋይህ እየደረሰባት ያለውን መከራ ተመልክተህ ብታስበኝና አገልጋይህን ሳትረሳት ወንድ ልጅ ብትሰጣት በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ለይሖዋ እሰጠዋለሁ፤ ራሱንም ምላጭ አይነካውም።”a (1 ሳሙ. 1:11) ሐና ያቀረበችው ልመና ምላሽ ያገኘ ሲሆን ወንድ ልጅ ወለደች። ይህ ምንኛ አስደስቷት ይሆን! ያም ቢሆን ለአምላክ የተሳለችውን ነገር አልረሳችም። ወንድ ልጅ ስትወልድ “ከይሖዋ የለመንኩት ነው” በማለት ተናግራለች።—1 ሳሙ. 1:20
-