-
ትዕቢት ውርደትን ያስከትላልመጠበቂያ ግንብ—2000 | ነሐሴ 1
-
-
16. ሳኦል ትዕግሥት እንደሌለው ያሳየው እንዴት ነው?
16 ይሁን እንጂ ከጊዜ በኋላ ሳኦል የነበረው ልክን የማወቅ ባሕርይ እልም ብሎ ጠፋ። ከፍልስጤማውያን ጋር ውጊያ ገጥሞ በነበረበት ጊዜ ሳሙኤል እስኪመጣና መሥዋዕት አቅርቦ አምላክን እስኪለምን ድረስ መጠበቅ ስለነበረበት ወደ ጌልገላ ሄደ። ሳሙኤል በተባለው ሰዓት ሳይመጣ በዘገየ ጊዜ ሳኦል በትዕቢት ተነሳስቶ የሚቃጠለውን መሥዋዕት ራሱ አቀረበ። መሥዋዕቱን አቅርቦ እንደጨረሰ ሳሙኤል መጣ። ሳሙኤልም “ያደረግኸው ምንድር ነው?” በማለት ጠየቀው። ሳኦልም “ሕዝቡ ከእኔ ተለይተው እንደ ተበታተኑ፣ አንተም በቀጠሮው እንዳልመጣህ . . . አየሁ፤ . . . ስለዚህም ሳልታገሥ የሚቃጠልን መሥዋዕት አሳረግሁ አለ።”—1 ሳሙኤል 13:8-12
17. (ሀ) እንዲሁ ከላይ ሲታይ ሳኦል የፈጸመው ድርጊት ትክክል ሊመስል የሚችለው ለምንድን ነው? (ለ) ይሖዋ ትዕግሥት የማጣት እርምጃ የወሰደውን ሳኦልን ያወገዘው ለምንድን ነው?
17 እንዲሁ ከላይ ሲታይ ሳኦል ያደረገው ነገር ትክክል ሊመስል ይችላል። ደግሞም የአምላክ ሕዝቦች በነበሩበት ተስፋ አስቆራጭ ሁኔታ የተነሳ “ተጨንቀው” ይንቀጠቀጡ ነበር። (1 ሳሙኤል 13:6, 7) እርግጥ ነው፣ ሁኔታዎች የሚፈቅዱ ከሆነ በራስ ተነሳሽነት አንድ ነገር ማድረጉ ምንም ስህተት የለበትም።d ሆኖም ይሖዋ ልብን ማንበብና የተነሳሳንበትን ውስጣዊ ግፊት ማወቅ እንደሚችል አትዘንጋ። (1 ሳሙኤል 16:7) በመሆኑም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በቀጥታ ባይጠቀስም ሳኦልን በሚመለከት አንድ ያየው ነገር መኖር አለበት። ለምሳሌ ያህል ሳኦል ትዕግሥት ያጣው በውስጡ ባደረበት ትዕቢት እንደሆነ ይሖዋ ተመልክቶ ሊሆን ይችላል። ምናልባት የእስራኤል ንጉሥ የሆነው ሳኦል ዕድሜው ከመግፋቱ የተነሳ እያዘገመ እንደሚመጣ አድርጎ የተመለከተውን ነቢይ መጠበቁ አበሳጭቶት ሊሆን ይችላል! ያም ሆነ ይህ የሳሙኤል መዘግየት ነገሮችን በራሱ መንገድ ማከናወንና የተሰጠውን ጥብቅ መመሪያም ችላ ብሎ ማለፍ እንደሚያስችለው ሆኖ ተሰምቶት ይሆናል። ታዲያ ውጤቱ ምን ሆነ? ሳሙኤል ጎሽ አበጀህ አላለውም። ከዚያ ይልቅ “መንግሥትህ አይጸናም . . . እግዚአብሔርም ያዘዘህን አልጠበቅህምና” በማለት በቁጣ ተናግሮታል። (1 ሳሙኤል 13:13, 14) አሁንም ቢሆን ትዕቢት ውርደትን አስከትሏል።
-
-
ትዕቢት ውርደትን ያስከትላልመጠበቂያ ግንብ—2000 | ነሐሴ 1
-
-
d ለምሳሌ ያህል ፊንሐስ በአሥር ሺዎች ለሚቆጠሩ እስራኤላውያን ሕይወት መጥፋት ምክንያት የሆነው መቅሰፍት እንዲገታ ለማድረግ ፈጣን እርምጃ ወስዷል። እንዲሁም ዳዊት ከእርሱ ጋር ያሉ እርቧቸው የነበሩ ሰዎች ‘በእግዚአብሔር ቤት’ የሚገኘውን የተቀደሰ እንጀራ አብረውት እንዲበሉ ጋብዟቸዋል። አምላክ የሁለቱንም ድርጊት እንደ ትዕቢት ቆጥሮ አላወገዘውም።—ማቴዎስ 12:2-4፤ ዘኁልቁ 25:7-9፤ 1 ሳሙኤል 21:1-6
-