የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ‘የተሰበረና የተዋረደ ልብ’ ያላቸው ሰዎች ምሕረት በሚፈልጉበት ጊዜ
    መጠበቂያ ግንብ—2010 | ግንቦት 1
    • ዳዊት ራሱን ነፃ ለማድረግ ሰበብ እንዳይፈጥር ሲል ከዚህ ቀደም እረኛ የነበረውን የዳዊትን ልብ እንደሚነካ እርግጠኛ የሆነበትን አንድ ታሪክ ነገረው። ታሪኩ ስለ አንድ ባለጠጋና ስለ አንድ ድሃ የሚናገር ነበር። ባለጠጋው “እጅግ ብዙ በጎችና የቀንድ ከብቶች” የነበሩት ሲሆን ድሃው ግን “አንዲት ጠቦት” ብቻ ነበረችው። ባለጠጋው እንግዳ ስለመጣበት ምግብ ማዘጋጀት ፈለገ። ከራሱ በጎች መካከል ወስዶ ከማዘጋጀት ይልቅ ድሃው ያለችውን አንዲት ጠቦት ወሰደ። ዳዊት የተነገረው ታሪክ እውነት መስሎት መሆን አለበት በጣም ተቆጥቶ “ይህን ያደረገው ሰው ሞት ይገባዋል!” በማለት ተናገረ። ለምን? ዳዊት ምክንያቱን ሲናገር ‘ሐዘኔታ’ አላሳየም በማለት ገልጿል።a—ቁጥር ከ2-6

  • ‘የተሰበረና የተዋረደ ልብ’ ያላቸው ሰዎች ምሕረት በሚፈልጉበት ጊዜ
    መጠበቂያ ግንብ—2010 | ግንቦት 1
    • a በጥንት ጊዜ እንግዳ ሲመጣ ጠቦት ማረድ የተለመደ ነበር። ሆኖም ጠቦት መስረቅ ወንጀል ስለነበር እንዲህ ዓይነቱን ድርጊት የፈጸመ ሰው አራት እጥፍ መክፈል ይጠበቅበታል። (ዘፀአት 22:1) ዳዊት፣ ባለጠጋው ሰው ጠቦቱን ከድሃው መውሰዱ ርኅራኄ የጎደለው ድርጊት እንደፈጸመ የሚያሳይ እንደሆነ ተሰምቶት ነበር። ባለጠጋው ከድሃው ሰው ጠቦቱን መውሰዱ ቤተሰቡ የሚያገኘውን ወተት፣ ሱፍ ሌላው ቀርቶ ወደፊት ብዙ በጎችን ሊያረባበት የሚችልበትን አጋጣሚ ሁሉ ያሳጣዋል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ