-
የራስን ጥቅም የመሰዋትና በታማኝነት የመጣበቅ ምሳሌመጠበቂያ ግንብ—1997 | ኅዳር 1
-
-
ኤልሳዕ የተባለ አንድ ወጣት ገበሬ አንድ ቀን በዘወትር የእርሻ ሥራው ላይ ተሰማርቶ ሳለ በሕይወቱ ውስጥ ፈጽሞ ያልጠበቀው ነገር ገጠመው። እርሻውን እያረሰ ባለበት ወቅት የእስራኤል ዋነኛ ነቢይ የሆነው ኤልያስ ድንገት ሊጠይቀው መጣ። ‘ምን ፈልጎ ይሆን ሊጠይቀኝ የመጣው?’ ብሎ ሳያስብ አይቀርም። መልስ ለማግኘት ብዙ መጠበቅ አላስፈለገውም። ኤልያስ የነቢይነት ልብሱን ኤልሳዕ ላይ በመጣል አንድ ቀን ኤልሳዕ የእርሱ ተተኪ እንደሚሆን ጠቆመው። ኤልሳዕ ጥሪውን አቅልሎ አልተመለከተውም። ኤልሳዕ ወዲያው እርሻውን ትቶ የኤልያስ አገልጋይ ለመሆን ሄደ።—1 ነገሥት 19:19-21
-
-
የራስን ጥቅም የመሰዋትና በታማኝነት የመጣበቅ ምሳሌመጠበቂያ ግንብ—1997 | ኅዳር 1
-
-
ከኤልያስ ጋር እንዲሠራ ለልዩ አገልግሎት ግብዣ በቀረበለት ጊዜ ኤልሳዕ የእስራኤልን ዋነኛ ነቢይ ለማገልገል እርሻውን ወዲያውኑ ትቶ ሄደ። “በኤልያስ እጅ ላይ ውኃ ያፈስስ የነበረው” ተብሎ ይታወቅ ስለነበር አንዳንድ ሥራዎቹ ዝቅተኛ እንደነበሩ ከሁኔታው ለመረዳት ይቻላል።c (2 ነገሥት 3:11) የሆነ ሆኖ ኤልሳዕ ሥራውን እንደ መብት ቆጥሮታል፤ ከኤልያስ ጎንም በታማኝነት ተጣብቋል።
በዛሬው ጊዜ አብዛኞቹ የአምላክ አገልጋዮች ተመሳሳይ የሆነ የራስን ጥቅም የመሰዋት መንፈስ ያሳያሉ። አንዳንዶች ራቅ ባሉ ክልሎች ምሥራቹን ለመስበክ ወይም የቤቴል ቤተሰብ አባል ሆነው ለማገልገል ሲሉ “እርሻቸውን” ማለትም የሚተዳደሩበትን ሥራ ትተዋል። ሌሎች ደግሞ በማኅበሩ የግንባታ ፕሮጀክቶች ለመሥራት ወደ ባዕድ አገሮች ሄደዋል። ብዙዎች ዝቅተኛ ሥራዎች ሊባሉ የሚችሉትን በፈቃደኝነት ተቀብለዋል። ሆኖም ይሖዋን የሚያገለግል ማንኛውም ሰው የሚያከናውነው አገልግሎት ፈጽሞ አይናቅም። ይሖዋ በፈቃደኝነት እርሱን የሚያገለግሉትን ያደንቃል፤ የራስን ጥቅም የመሰዋት መንፈሳቸውንም ይባርካል።—ማርቆስ 10:29, 30
-