-
ብልጽግና እምነትህን ሊፈትነው ይችላልመጠበቂያ ግንብ—1993 | ሐምሌ 15
-
-
ምንም እንኳን አሳፍ የይሖዋን ጥሩነት ቢያውቅም አረማመዱ ከጽድቅ ጎዳና ሊወጣ ትንሽ ቀርቶት ነበር። ሁኔታው አድካሚ በሆነ የማራቶን ውድድር ወቅት እግሮቹ በበረዶ ላይ እንደሚንሸራተቱበት ያክል ነበር። እምነቱ ይህን ያህል ተዳክሞ የነበረው ለምንድን ነው? ስለዚህ ሲገልጽ እንዲህ አለ:- “ የኃጢአተኞችን ሰላም አይቼ በዓመፀኞች ቀንቼ ነበርና። ለሞታቸው መጣጣር የለውምና፤ ኃይላቸውም ጠንካራ ነው [ገላቸውም የሰባ ነውና የ1879 እትም ] እንደ ሰው በድካም አልሆኑም ከሰውም ጋር አልተገረፉም። [በሰው ድካም አልተገኙም። ከሰውም ጋር አልተሰቃዩም የ1879 እትም ]” — መዝሙር 73:3–5
-
-
ብልጽግና እምነትህን ሊፈትነው ይችላልመጠበቂያ ግንብ—1993 | ሐምሌ 15
-
-
ብዙ ክፉ ሰዎች ያላቸውን የተትረፈረፈ ምግብ እንዳይመገቡ የሚከለክላቸው የጤና ችግር የለባቸውም። “ገላቸውም የሰባ” ቦርጫቸውም ደግሞ የተንዘረጠጠ ነው። ከዚህም በተጨማሪ “በሰው ድካም አልተገኙም” ማለትም እንደተቀረው የሰው ዘር ለሕይወት የሚያስፈልጋቸውን ለማግኘት ቀና ደፋ ለማለት አይገደዱም። አሳፍ ክፉዎች ‘እንደሌላው ሰው አይንገላቱም’ ሲል ደምድሟል። በተለይም የአምላክ ሕዝቦች በክፉው የሰይጣን ዓለም ውስጥ የይሖዋን የጽድቅ ሥርዓት አጥብቀው በመከተላቸው ከሚመጡባቸው መከራዎች ክፉዎች ያመልጣሉ። — 1 ዮሐንስ 5:19
-