-
ብልጽግና እምነትህን ሊፈትነው ይችላልመጠበቂያ ግንብ—1993 | ሐምሌ 15
-
-
አሳፍ አስተሳሰቡ የተሳሳተ መሆኑን በመገንዘብ በመጨረሻ እንዲህ አለ:- “ እንደዚህ ብዬ ብናገር ኖሮ፣ እነሆ፣ የልጆችህን ትውልድ በበደልሁ ነበር። አውቅም ዘንድ አሰብሁ፣ ይህ ግን በፊቴ ችግር ነበር። ወደ እግዚአብሔር መቅደስ እስክገባ ድረስ፣ ፍጻሜአቸውንም እስካስተውል ድረስ። በድጥ ስፍራ አስቀመጥሃቸው፣ ወደ ጥፋትም ጣልሃቸው። እንዴት ለጥፋት ሆኑ! በድንገት አለቁ ስለ ኃጢአታቸውም ጠፉ። ከሕልም እንደሚነቃ፣ አቤቱ፣ ስትነቃ ምልክታቸውን ታስነውራለህ።” — መዝሙር 73:15–20
-
-
ብልጽግና እምነትህን ሊፈትነው ይችላልመጠበቂያ ግንብ—1993 | ሐምሌ 15
-
-
አምላክ ክፉዎችን “በድጥ ስፍራ” እንዳስቀመጣቸው አሳፍ ተገነዘበ። ሕይወታቸው ያተኮረው በቁሳዊ ሀብት ዙሪያ በመሆኑ ድንገተኛ ውድቀት ሊያጋጥማቸው ይችላል። ቢቆይ ቢቆይ በእርጅናቸው ዘመን ሞት ይነጥቃቸዋል፤ በማጭበርበር ያከማቹት ሀብት ዕድሜያቸውን ለማራዘም ዋስትና አይሆናቸውም። (መዝሙር 49:6–12) ብልጽግናቸው ፈጥኖ እንደሚያልፍ ሕልም ይሆናል። ከማርጀታቸውም በፊት እንኳ ፍትሕ ያገኛቸውና የዘሩትን ሊያጭዱ ይችላሉ። (ገላትያ 6:7) ለብቸኛው ረዳታችው ጀርባቸውን ስለሰጡት ረዳት አልባና ተስፋ የለሾች ሆነዋል። ይሖዋ በእነርሱ ላይ እርምጃ ሲወስድባቸው “ምልክታቸውን” ማለትም ያላቸውን ድምቀት እና ደረጃ ከጉዳይ አይጥፈውም።
-