-
እምነት ከማጣት ተጠበቁመጠበቂያ ግንብ—1998 | ሐምሌ 15
-
-
‘ልባችሁን አታደንድኑ’
13. ጳውሎስ ምን ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል? መዝሙር 95ንስ የተጠቀመበት እንዴት ነው?
13 ጳውሎስ ዕብራውያን ክርስቲያኖች ስላገኙት ሞገስ ከገለጸ በኋላ የሚከተለውን ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል:- “ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ እንደሚል:- ዛሬ ድምፁን ብትሰሙት፣ . . . በምድረ በዳ በፈተና ቀን በማስመረር እንደ ሆነ፣ ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ [“አታደንድኑ፣” NW]።” (ዕብራውያን 3:7, 8) ጳውሎስ እየጠቀሰ ያለው ከ95ኛው መዝሙር ስለነበር “መንፈስ ቅዱስ እንደሚል” ብሎ ለመናገር ይችላል።b (መዝሙር 95:7, 8፤ ዘጸአት 17:1-7) ቅዱሳን ጽሑፎች በአምላክ ቅዱስ መንፈስ አነሳሽነት የተጻፉ ናቸው።—2 ጢሞቴዎስ 3:16
14. እስራኤላውያን ይሖዋ ላደረገላቸው ነገር ምን ምላሽ ሰጡ? ለምንስ?
14 እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት ነፃ ከወጡ በኋላ ከይሖዋ ጋር በቃል ኪዳን የታሰረ ዝምድና በመመሥረት ታላቅ ክብር አግኝተዋል። (ዘጸአት 19:4, 5፤ 24:7, 8) ይሁን እንጂ አምላክ ያደረገላቸውን ከማድነቅ ይልቅ ብዙም ሳይቆዩ ዓመፀኞች ሆኑ። (ዘኁልቁ 13:25–14:10) ይህ ሊሆን የቻለው እንዴት ነው? ጳውሎስ ልባቸውን በማደንደናቸው ምክንያት እንደሆነ ገልጿል። የአምላክን ቃል ያስተውልና ጥሩ ምላሽ ይሰጥ የነበረ ልብ እንዴት ደንዳና ሊሆን ይችላል? ይህን ለመከላከልስ ምን ማድረግ አለብን?
15. (ሀ) ጥንትም ሆነ ዛሬ ‘የአምላክ ድምፅ’ ሲሰማ የቆየው እንዴት ነው? (ለ) ‘የአምላክን ድምፅ’ አስመልክቶ ራሳችንን ምን ብለን መጠየቅ አለብን?
15 ጳውሎስ ማስጠንቀቂያውን የጀመረው “ድምፁን ብትሰሙት” በሚል ሐረግ ነው። አምላክ በሙሴና በሌሎች ነቢያት በኩል ለሕዝቡ ይናገር ነበር። ከዚያም ይሖዋ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ተናግሯል። (ዕብራውያን 1:1, 2) ዛሬ በመንፈስ አነሳሽነት የተጻፈው ሙሉው የአምላክ ቃል ማለትም መጽሐፍ ቅዱስ አለን። በተጨማሪም መንፈሳዊ ‘ምግብ በተገቢው ጊዜ’ የሚያቀርብ “ታማኝና ልባም ባሪያ” አለን። (ማቴዎስ 24:45-47) ስለዚህ ይሖዋ አሁንም እየተናገረ ነው። ታዲያ እየሰማነው ነው? ለምሳሌ ያህል ስለ አለባበሳችንና አጋጌጣችን ወይም ስለ መዝናኛና ሙዚቃ ምርጫችን ለተሰጠን ምክር ምላሽ እየሰጠን ያለነው እንዴት ነው? ትኩረት በመስጠትና የተነገረውን በመታዘዝ ‘እንደምንሰማ’ እናሳያለንን? ለምንሠራቸው ነገሮች ሰበብ የመፍጠር ወይም የሚሰጠንን ምክር የመቃወም ልማድ ካለን ራሳችንን ረቂቅ ለሆነ አደጋ በማጋለጥ ልባችን ደንዳና እንዲሆን መንገድ እየከፈትንለት ነው ማለት ነው።
16. ልባችን ደንዳና ሊሆን የሚችልበት አንዱ መንገድ ምንድን ነው?
16 በተጨማሪም ማድረግ የምንችለውንና ማድረግ ያለብንን ነገር ከማድረግ ወደ ኋላ የምንል ከሆነ ልባችን ደንዳና ሊሆን ይችላል። (ያዕቆብ 4:17) ይሖዋ ለእስራኤላውያን ብዙ ነገር ቢያደርግላቸውም እምነት ማሳየታቸውን አቆሙ፣ በሙሴ ላይ ዓመፁ፣ ስለ ከነዓን የሰሙትን መጥፎ ዜና ለማመን መረጡ፣ እንዲሁም ወደ ተስፋይቱ ምድር ለመግባት አሻፈረን አሉ። (ዘኁልቁ 14:1-4) ስለዚህ ይሖዋ የዚያ እምነት የለሽ ትውልድ አባላት ሞተው እስኪያልቁ ድረስ 40 ዓመታት ሙሉ በምድረ በዳ እንዲቆዩ ወሰነ። አምላክ ስለጠላቸው እንዲህ ብሎ ተናገረ:- “ዘወትር በልባቸው ይስታሉ መንገዴን ግን አላወቁም አልሁ፤ እንዲሁ:- ወደ ዕረፍቴ አይገቡም ብዬ በቊጣዬ ማልሁ።” (ዕብራውያን 3:9-11) ይህ ለእኛ ምን ትምህርት ይሰጠናል?
-
-
እምነት ከማጣት ተጠበቁመጠበቂያ ግንብ—1998 | ሐምሌ 15
-
-
19. ምክርን አለመስማት የትኞቹን ከባድ መዘዞች ያስከትላል? በምሳሌ አስረዳ።
19 ስለዚህ ይሖዋ በቃሉና በታማኙ ባሪያው ክፍል የሚሰጠንን ምክር ችላ በማለት ‘ድምፁን ያለመስማት’ ልማድ ካለን ብዙም ሳይቆይ ልባችን መጅ ያወጣል እንዲሁም ደንዳና ይሆናል። ለምሳሌ ያህል ያልተጋቡ ወንድና ሴት ከልክ በላይ በመቀራረብ ማድረግ የሌለባቸውን ድርጊት ፈጽመው ይሆናል። ጉዳዩን ችላ ቢሉትስ? ቀደም ሲል ያደረጉትን ነገር ደግመው እንዳያደርጉ ሊጠብቃቸው ይችላል? ከዚህ ይልቅ ያንኑ ድርጊት ደግመው እንዲፈጽሙ በር አይከፍትላቸውምን? በተመሳሳይም የባሪያው ክፍል በሙዚቃ፣ በመዝናኛና በሌሎችም ነገሮች ረገድ መራጮች እንድንሆን ምክር ሲለግሰን በአድናቆት ተቀብለን አስፈላጊውን ማስተካከያ እናደርጋለንን? ጳውሎስ ‘መሰብሰባችንን እንዳንተው’ ማሳሰቢያ ሰጥቶናል። (ዕብራውያን 10:24, 25) ይህ ምክር ቢሰጥም አንዳንዶች ለክርስቲያናዊ ስብሰባዎች ብዙም ትኩረት አይሰጡም። ከአንዳንድ ስብሰባዎች መቅረት ወይም አንዳንዶቹን ስብሰባዎች ከናካቴው እርግፍ አድርጎ መተው ምንም ችግር እንደሌለው ሆኖ ይሰማቸው ይሆናል።
-
-
እምነት ከማጣት ተጠበቁመጠበቂያ ግንብ—1998 | ሐምሌ 15
-
-
b ጳውሎስ “መሪባህ” እና “ማሳህ” የሚሉትን የዕብራይስጥ ቃላት “መጣላት” እና “መፈታተን” ብሎ ከሚተረጉመው ከግሪኩ የሴፕቱጀንት ትርጉም ጠቅሶ መጻፉን ከሁኔታው ለመረዳት ይቻላል። ኒው ዮርክ በሚገኘው የመጠበቂያ ግንብ መጽሐፍ ቅዱስና ትራክት ማኅበር የታተመውን ቅዱሳን ጽሑፎችን ጠለቅ ብሎ ማስተዋል የተባለውን መጽሐፍ ጥራዝ 2 ገጽ 350ና 379 ተመልከት።
-