-
ሥራችሁ እሳቱን ይቋቋም ይሆን?መጠበቂያ ግንብ—1998 | ኅዳር 1
-
-
4. (ሀ) በክርስቲያናዊው የግንባታ ሥራ ውስጥ ጳውሎስ የነበረው ሚና ምንድን ነው? (ለ) ኢየሱስም ሆነ አድማጮቹ የጥሩ መሠረትን አስፈላጊነት ያውቁ ነበር ሊባል የሚቻለው ለምንድን ነው?
4 አንድ ሕንፃ ምንም ሳይሆን ለረዥም ጊዜ እንዲቆይ ከተፈለገ ጥሩ መሠረት ሊኖረው ይገባል። በመሆኑም ጳውሎስ “የእግዚአብሔር ጸጋ እንደ ተሰጠኝ መጠን እንደ ብልሃተኛ የአናጺ [“የሥራ፣” NW] አለቃ መሠረትን መሠረትሁ” ሲል ጽፏል። (1 ቆሮንቶስ 3:10) ኢየሱስ ክርስቶስም ጠንካራ መሠረት መርጦ ቤቱን ስለገነባ ሰው የሚገልጽ ተመሳሳይ ምሳሌ ተናግሯል። ይህ ቤት በጠንካራ መሠረት ላይ ስለተገነባ በማዕበል ከመወሰድ ሊተርፍ ችሏል። (ሉቃስ 6:47–49) ኢየሱስ መሠረት ምን ያህል ወሳኝነት ያለው ነገር መሆኑን ጠንቅቆ ያውቃል። ይሖዋ ምድርን በመሠረተ ጊዜ አብሮት ነበር።a (ምሳሌ 8:29–31) የኢየሱስ አድማጮችም ቢሆኑ ጥሩ መሠረት አስፈላጊ መሆኑን ያውቁ ነበር። በፍልስጤም ምድር አልፎ አልፎ የሚከሰቱትን የጎርፍና የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች ለመቋቋም የሚችሉት በጥሩ መሠረት ላይ የተገነቡ ቤቶች ብቻ ነበሩ። ሆኖም ጳውሎስ በአእምሮው ይዞት የነበረው መሠረት ምን ነበር?
-
-
ሥራችሁ እሳቱን ይቋቋም ይሆን?መጠበቂያ ግንብ—1998 | ኅዳር 1
-
-
a ‘የምድር መሠረት’ የሚለው ሐሳብ ምድርን ደግፈው የያዟትን የተፈጥሮ ኃይላት እንዲሁም ቦታ ቦታቸውን ይዘው የሚገኙትን ሰማያዊ አካላት በሙሉ ሊያመለክት ይችላል። በተጨማሪም ምድር ራሷ የተሠራችው ለዘላለም “እንዳትናወጥ” ወይም እንዳትጠፋ ሆና ነው።—መዝሙር 104:5
-