-
ቤተሰባችሁን ጎጂ ከሆኑ ተጽዕኖዎች ጠብቁለቤተሰብ ደስታ ቁልፉ ምንድን ነው?
-
-
19. ቤተሰቦች የሚያስደስቱና የሚያዝናኑ ነገሮች ማድረጋቸው ኃጢአት እንዳልሆነ የትኞቹ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሳሌዎች ያሳያሉ?
19 መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስደስትና የሚያዝናና ነገር ማድረግን ያወግዛልን? በፍጹም! መጽሐፍ ቅዱስ “ለመሳቅም ጊዜ አለው . . . ለመዝፈንም [“ለመጨፈርም፣” የ1980 ትርጉም] ጊዜ አለው” ይላል።b (መክብብ 3:4) በጥንት እስራኤል ዘመን የአምላክ ሕዝቦች በዘፈን፣ በጭፈራ፣ በጨዋታና በእንቆቅልሾች ይዝናኑ ነበር። ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድ ትልቅ የሠርግ ድግስ ላይና ማቴዎስ ሌዊ ባዘጋጀለት “ታላቅ ግብዣ” ላይ ተገኝቶ ነበር። (ሉቃስ 5:29፤ ዮሐንስ 2:1, 2) ኢየሱስ ሌሎችን ደስታ የሚያሳጣ እንዳልነበረ በግልጽ መረዳት ይቻላል። በቤተሰባችሁ ውስጥ ሳቅና ጨዋታ ፈጽሞ እንደ ኃጢአት መቆጠር የለበትም!
-
-
ቤተሰባችሁን ጎጂ ከሆኑ ተጽዕኖዎች ጠብቁለቤተሰብ ደስታ ቁልፉ ምንድን ነው?
-
-
b እዚህ ላይ “መሳቅ” ተብሎ የተተረጎመው የዕብራይስጥ ቃል “መጫወት፣” “ማዝናናት፣” “እንደ ግብዣ ያለ አስደሳች ዝግጅት ማድረግ” ወይም ደግሞ “የሚያስደስት ነገር ማድረግ” ተብሎ በሌሎች መንገዶችም ሊተረጎም ይችላል።
-