የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • የይሖዋ ወዳጅ መሆን ትችላለህ
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 6. ይሖዋ ለወዳጆቹ የሚያደርጋቸው ነገሮች

      ይሖዋ ወዳጆቹ ያጋጠሟቸውን ችግሮች መቋቋም እንዲችሉ ይረዳቸዋል። ቪዲዮውን ተመልከቱ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      ቪዲዮ፦ ይሖዋ ብዙ ነገር አድርጎልኛል (3:20)

      • ይሖዋ በቪዲዮው ላይ የታየችው ሴት የነበራትን አሉታዊ አስተሳሰብና ስሜት እንድታሸንፍ የረዳት እንዴት ነው?

      ኢሳይያስ 41:10, 13⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      • ይሖዋ ለወዳጆቹ ሁሉ ምን እንደሚያደርግላቸው ቃል ገብቷል?

      • ይሖዋ ጥሩ ወዳጅ የሚሆንህ ይመስልሃል? እንዲህ ብለህ የመለስከው ለምንድን ነው?

      የቅርብ ጓደኛሞች ሲረዳዱ የሚያሳዩ ሥዕሎች፦ 1. አንድ ሰው ሌላን ሰው ትልቅ ጠረጴዛ ማንቀሳቀስ ሲያግዘው 2. አንዲት ሴት ያሳሰባትን ነገር ለሌላ ሴት ስትነግራት 3. አንድ ሰው ከዘራ ይዞ የሚራመድን ሌላ ሰው ደግፎት

      የቅርብ ወዳጆችህ በሚያስፈልግህ ጊዜ ሁሉ ይረዱሃል። ይሖዋም ልክ እንደዚሁ ያደርጋል

  • የይሖዋ ወዳጅ መሆን ትችላለህ
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
  • ምሥራቹን ለሌሎች መናገር የምትችለው እንዴት ነው?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 3. ይሖዋ ከአንተ ጋር ይሆናል

      አንዳንዶች መስበክ ቢፈልጉም ሌሎች ለእነሱ ስለሚኖራቸው አመለካከት ወይም ስለሚሰጧቸው ምላሽ ሲያስቡ ፍርሃት ይሰማቸዋል።

      • የተማርከውን ነገር ለሌሎች መናገር ያስፈራሃል? እንዲህ የሚሰማህ ለምንድን ነው?

      ቪዲዮውን ተመልከቱ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      ቪዲዮ፦ ይሖዋ ድፍረት እንዲሰጠኝ ጸለይኩ (4:05)

      • በቪዲዮው ላይ የታዩት ወጣት የይሖዋ ምሥክሮች ፍርሃታቸውን እንዲያሸንፉ የረዳቸው ምንድን ነው?

      ኢሳይያስ 41:10⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      • መስበክ የሚያስፈራህ ከሆነ መጸለይህ የሚረዳህ እንዴት ነው?

      ይህን ታውቅ ነበር?

      ብዙ የይሖዋ ምሥክሮች ቀደም ሲል መቼም ቢሆን ምሥራቹን ለሌሎች መናገር እንደማይችሉ ይሰማቸው ነበር። ለምሳሌ ያህል፣ ሰርጌ የተባለ ሰው የዋጋ ቢስነት ስሜት ስለሚሰማው ሰዎችን ቀርቦ ማነጋገር ይከብደው ነበር። በኋላ ግን መጽሐፍ ቅዱስን መማር ጀመረ። እንዲህ ብሏል፦ “ፍርሃት ቢያድርብኝም የተማርኳቸውን ነገሮች ለሌሎች መናገር ጀመርኩ። በጣም የሚያስገርመው፣ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ለሌሎች መናገሬ በራስ የመተማመን ስሜቴን ከፍ አደረገልኝ። እንዲሁም የማምንባቸው አዳዲስ እውነቶች በልቤ ውስጥ ሥር እንዲሰዱ አደረጋቸው።”

  • ለመጠመቅ ዝግጁ ነህ?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 6. ይሖዋ እንደሚረዳህ እምነት ይኑርህ

      ወጣቷ ሴት በዕድሜ ለገፉ ሴት ስትሰብክ። የመጽሐፍ ቅዱስ አስተማሪዋ አብራት አገልግሎት ወጥታለች

      ይሖዋ እሱን ማስደሰት እንድትችል ይረዳሃል። ቪዲዮውን ተመልከቱ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      ቪዲዮ፦ ይሖዋ አምላክ ይረዳችኋል (2:50)

      • በቪዲዮው ላይ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪው ከመጠመቅ ወደኋላ ብሎ የነበረው ለምንድን ነው?

      • በይሖዋ ላይ ያለውን እምነት እንዲያጠናክር የረዳው ምን ማወቁ ነው?

      ኢሳይያስ 41:10, 13⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      • ራስህን ስትወስን የገባኸውን ቃል መጠበቅ እንደምትችል እንድትተማመን የሚያደርግህ ምንድን ነው?

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ