-
አንተንም የሚመለከቱ አጽናኝ ትንቢታዊ ቃላትየኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 2
-
-
24, 25. ይሖዋ ቂሮስን በድጋሚ በመጥቀስ ምን ብሏል? ይህስ የትኛውን ሌላ ትንቢት ያስታውሰናል?
24 ይሖዋ በድጋሚ ስለ ቂሮስ በመጥቀስ እንዲህ ይላል:- “አንዱን ከሰሜን አስነሣሁት፤ እርሱም ይመጣል፤ ከፀሐይ መውጫ የሚመጣው፣ ስሜን የሚጠራ ነው፤ ሸክላ ሠሪ ዐፈር እንደሚረግጥ፣ አለቆችን እንዲሁ እንደ ጭቃ ይረግጣል።” (ኢሳይያስ 41:25 አ.መ.ት)d ይሖዋ ነገሮችን ዳር ማድረስ ይችላል፤ የአሕዛብ አማልክት ግን ይህን ማድረግ አይችሉም። ቂሮስን “ከፀሐይ መውጫ” ማለትም ከምሥራቅ በማምጣት የመተንበይ ችሎታ እንዳለውና ወደፊት የሚከናወኑት ነገሮች ከትንቢቱ ጋር በሚስማማ መንገድ እንዲፈጸሙ ማድረግ የሚችል መሆኑን በተግባር ያሳያል።
25 እነዚህ ቃላት ሐዋርያው ዮሐንስ በእኛ ዘመን እርምጃ ለመውሰድ ስለሚነሡ ነገሥታት የሰጠውን ትንቢታዊ መግለጫ ያስታውሱናል። በራእይ 16:12 ላይ “ከፀሐይም መውጫ ለሚመጡ ነገሥታት” መንገድ እንደሚዘጋጅላቸው ተገልጾልናል። እነዚህ ነገሥታት ከይሖዋ አምላክና ከኢየሱስ ክርስቶስ ሌላ ማንም ሊሆኑ አይችሉም። ቂሮስ ከረጅም ጊዜ በፊት የአምላክን ሕዝብ ነፃ እንዳወጣ ሁሉ ከእርሱ እጅግ የላቀ ኃይል ያላቸው እነዚህ ነገሥታት የይሖዋን ጠላቶች ጨርሰው በማጥፋት የአምላክን ሕዝብ እየመሩ ከታላቁ መከራ ወደ አዲሱ ዓለም ያሻግሩታል።—መዝሙር 2:8, 9፤ 2 ጴጥሮስ 3:13፤ ራእይ 7:14-17
-
-
አንተንም የሚመለከቱ አጽናኝ ትንቢታዊ ቃላትየኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 2
-
-
d የቂሮስ የትውልድ አገር ከባቢሎን በስተ ምሥራቅ ቢሆንም በከተማዋ ላይ የመጨረሻውን ጥቃት ሊሰነዝር የመጣው ግን ከሰሜን ማለትም ከትንሿ እስያ ነበር።
-