የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • አንድን ቅዱስ ምሥጢር መፍታት
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 2. (ሀ) ኢየሱስ ራሱን የገለጸው እንዴት ባለ የማዕረግ ስም ነው? (ለ) ይሖዋ “የመጀመሪያና የመጨረሻ እኔ ነኝ” ሲል ምን ማለቱ ነው? (ሐ) “የመጀመሪያውና የመጨረሻው” የሚለው የኢየሱስ የማዕረግ ስም የሚያመለክተው ምንን ነው?

      2 ይሁን እንጂ አድናቆታችን ከልክ ወዳለፈ ፍርሐትና መርበትበት መድረስ አይኖርበትም። ሐዋርያው ቀጥሎ እንደሚነግረን ኢየሱስ ዮሐንስን አበረታቶት ነበር። “ቀኝ እጁንም ጫነብኝ፣ እንዲህም አለኝ፣ ‘አትፍራ፣ ፊተኛውና መጨረሻው ሕያውም እኔ ነኝ።’” (ራእይ 1:17ለ, 18ሀ) ይሖዋ በ⁠ኢሳይያስ 44:6 ላይ የራሱን ደረጃ ሲገልጽ “እኔ ፊተኛ ነኝ፣ እኔም ኋለኛ ነኝ፣ ከእኔ ሌላም አምላክ የለም” ብሎ ነበር።a ኢየሱስ ራሱን “ፊተኛውና መጨረሻው” ሲል ራሱን ከታላቁ ፈጣሪ ከይሖዋ ጋር ማስተካከሉ አልነበረም። አምላክ የሰጠውን የማዕረግ ስም መጠቀሙ ነበር። ይሖዋ በኢሳይያስ ላይ የተናገረው ቃል በእውነተኛ አምላክነት ደረጃው ረገድ ያለውን ብቸኛና ልዩ ቦታ የሚያመለክት ነበር። ይሖዋ የዘላለም አምላክ ሲሆን ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም። (1 ጢሞቴዎስ 1:17) ኢየሱስ ግን በራእይ ላይ ያለውን ቃል የተናገረው የተሰጠውን የማዕረግ ስም ለመጥቀስና ስለተሰጠው ልዩ ዓይነት ትንሣኤ ለማመልከት ነበር።

  • አንድን ቅዱስ ምሥጢር መፍታት
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • a በጥንቱ የዕብራይስጥ ጽሑፍ ውስጥ በ⁠ኢሳይያስ 44:6 ላይ “የመጀመሪያ” እና “የመጨረሻ” በሚሉት ቃላት መጨረሻ ላይ “ው” የሚለው ጠቃሽ አመልካች አይገኝም። ኢየሱስ ስለራሱ በተናገረበት በጥንቱ የግሪክኛ ጽሑፍ በ⁠ራእይ 1:17 ላይ ግን “ው” የሚል ጠቃሽ አመልካች አለ። ስለዚህ የሰዋስው አገባቡ እንደሚያመለክተው ራእይ 1:17 የማዕረግ ስምን የሚያመለክት ሲሆን ኢሳይያስ 44:6 ግን የይሖዋን አምላክነት የሚያመለክት ነው።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ