-
ይሖዋ—‘ጻድቅ አምላክና አዳኝ’የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 2
-
-
24, 25. (ሀ) ይሖዋ ምን ጥሪ አቅርቧል? የገባው ቃል ፍጻሜውን ማግኘቱ የማይቀረው ለምንድን ነው? (ለ) ይሖዋ ምን መጠየቁ ተገቢ ነው?
24 የይሖዋ ምሕረት የሚከተለውን ጥሪ እንዲያቀርብ ገፋፍቶታል:- “እናንተ የምድር ዳርቻ ሁሉ፣ እኔ አምላክ ነኝና፣ ከእኔም በቀር ሌላ የለምና ወደ እኔ ዘወር በሉ ትድኑማላችሁ። ቃሌ ከአፌ በጽድቅ ወጥታለች፣ አትመለስም:- ጉልበት ሁሉ ለእኔ ይንበረከካል፣ ምላስም ሁሉ በእኔ ይምላል ብዬ በራሴ ምያለሁ። ስለ እኔም:- በእግዚአብሔር ዘንድ ብቻ ጽድቅና ኃይል አለ፣ ወደ እርሱም ሰዎች ይመጣሉ፣ በእርሱም ላይ የተቈጡ ሁሉ ያፍራሉ። የእስራኤልም ዘር ሁሉ በእግዚአብሔር ይጸድቃሉ፣ ይመካሉም ይባላል።” —ኢሳይያስ 45:22-25
-
-
ይሖዋ—‘ጻድቅ አምላክና አዳኝ’የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 2
-
-
26.ከሁሉም ብሔራት የተውጣጡ “እጅግ ብዙ ሰዎች” ይሖዋ ወደ እሱ ዘወር እንዲሉ ላቀረበው ጥሪ ምላሽ እየሰጡ ያሉት እንዴት ነው?
26 ይሁንና አምላክ ወደ እሱ ዘወር እንዲሉ ጥሪ ያቀረበው በጥንቷ ባቢሎን ለነበሩት ምርኮኞች ብቻ አይደለም። (ሥራ 14:14, 15፤ 15:19፤ 1 ጢሞቴዎስ 2:3, 4) ይህ ጥሪ አሁንም እየቀረበ ሲሆን ከሁሉም ብሔራት የተውጣጡ “እጅግ ብዙ ሰዎች” ጥሪውን በመቀበል “ለአምላካችንና ለበጉ [ለኢየሱስ] ማዳን ነው” ሲሉ አውጀዋል። (ራእይ 7:9, 10፤ 15:4) በየዓመቱ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ አዳዲስ ሰዎች የአምላክን ሉዓላዊነት ሙሉ በሙሉ በመቀበልና ከእሱ ጎን የተሰለፉ መሆናቸውን በይፋ በማሳወቅ ወደ ይሖዋ ዘወር እያሉ በመሆኑ የእጅግ ብዙ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ነው። እነዚህ ሰዎች “የአብርሃም ዘር” ለሆኑት መንፈሳዊ እስራኤላውያን በታማኝነት ድጋፍ ያደርጋሉ። (ገላትያ 3:29) በዓለም ዙሪያ “በእግዚአብሔር ዘንድ ብቻ ጽድቅና ኃይል አለ” ብለው በማወጅ ለይሖዋ የጽድቅ አገዛዝ ከፍተኛ ፍቅር እንዳላቸው ያሳያሉ።a ሐዋርያው ጳውሎስ ለሮሜ ሰዎች በጻፈው መልእክቱ ኢሳይያስ 45:23ን ከሰፕቱጀንት ትርጉም ላይ በመጥቀስ ሕይወት ያለው ሁሉ በመጨረሻ የአምላክን ሉዓላዊነት አምኖ እንደሚቀበልና ስሙን ለዘላለም እንደሚያመሰግን አመልክቷል።—ሮሜ 14:11፤ ፊልጵስዩስ 2:9-11፤ ራእይ 21:22-27
-
-
ይሖዋ—‘ጻድቅ አምላክና አዳኝ’የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 2
-
-
a የዕብራይስጡ ጽሑፍ እዚህ ላይ የገባውን “ጽድቅ” የሚለውን ቃል የገለጸው በብዙ ቁጥር ነው። ይህ ቃል በብዙ ቁጥር መገለጹ የይሖዋ ጽድቅ ማለቂያ የሌለው መሆኑን ያመለክታል።
-