-
“ያለህን አጽንተህ ያዝ”ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
12. በፊልድልፍያ የነበረው የአይሁድ ምኩራብ አባሎች ከመካከላቸው አንዳንዶቹ በከተማቸው ለነበረው የክርስቲያኖች ማህበረሰብ እንደ ሰገዱ ሲያውቁ የደነገጡት ለምንድን ነው?
12 በፊልድልፍያ የነበረው የአይሁድ ምኩራብ አባሎች በመካከላቸው የነበሩ አንዳንድ ሰዎች በከተማው ውስጥ ለነበረው የክርስቲያኖች ማኅበረሰብ ‘ሲሰግዱ’ ማየታቸው ሳያስደነግጣቸው አልቀረም። በጉባኤው ውስጥ ያሉ አይሁዳውያን ያልሆኑ ብዙ ክርስቲያኖች እንደሚኖሩ የተረጋገጠ ስለሆነ አይሁዳውያን ለክርስቲያኖች ሳይሆን ክርስቲያኖች ለአይሁዳውያን ተጎንብሰው ይሰግዳሉ ብለው ሳይጠብቁ አልቀረም። ለምን ቢባል ኢሳይያስ የሚከተለውን ትንቢት ተናግሮ ነበር። “[አይሁዳውያን ያልሆኑ] ነገሥታትም አሳዳጊ አባቶችሽ [ለአይሁድ ሕዝብ] ይሆናሉ፣ እተጌዎቻቸውም ሞግዚቶችሽ ይሆናሉ፤ ግምባራቸውንም ወደ ምድር ዝቅ አድርገው ይሰግዱልሻል።” (ኢሳይያስ 49:23፤ 45:14፤ 60:14) ዘካርያስም ከዚህ ጋር የሚመሳሰል ትንቢት ተናግሮ ነበር:- “በዚያ ዘመን ከአሕዛብ ቋንቋ ሁሉ አሥር ሰዎች የአንዱን አይሁዳዊ ሰው ልብስ ዘርፍ ይዘው:- እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር እንዳለ ሰምተናልና ከእናንተ ጋር እንሂድ ይላሉ።” (ዘካርያስ 8:23) አዎ፣ አይሁድ ያልሆኑ ሰዎች ለአይሁዳውያን ይሰግዳሉ እንጂ አይሁዳውያን አይሁድ ላልሆኑ ሰዎች አይሰግዱም ማለት ነው።
-
-
“ያለህን አጽንተህ ያዝ”ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
14. ኢሳይያስ 49:23 እና ዘካርያስ 8:23 በዘመናችን በጉልህ የተፈጸሙት እንዴት ነው?
14 በዘመናችንም እንደ ኢሳይያስ 49:23 እና ዘካርያስ 8:23 የመሰሉት ትንቢቶች በጉልህ ሁኔታ ተፈጽመዋል። የዮሐንስ ክፍል አባሎች ባከናወኑት የስብከት ሥራ ምክንያት በጣም ብዙ ሰዎች በተከፈተው በር በኩል ወደ መንግሥቱ አገልግሎት ገብተዋል።b ከእነዚህ ሰዎች አብዛኞቹ የመጡት በሐሰት መንፈሣዊ እሥራኤል ነኝ ከምትለው ከሕዝበ ክርስትና ነው። (ከሮሜ 9:6 ጋር አወዳድር።) እነዚህ ሰዎች የእጅግ ብዙ ሰዎች ክፍል እንደመሆናቸው መጠን በኢየሱስ ቤዛዊ ደም በማመን ልብሳቸውን አጥበው አንጽተዋል። (ራእይ 7:9, 10, 14) የክርስቶስን ንጉሣዊ አገዛዝ ስለሚታዘዙ የዚህችን መንግሥት በረከት በዚህችው ምድር ላይ ለመውረስ ተስፋ ያደርጋሉ። አምላክ ከኢየሱስ ቅቡዓን ወንድሞች ጋር እንዳለ ስለ ሰሙ በመንፈሳዊ አባባል ወደ እነርሱ ሄደው ይሰግዱላቸዋል። እነዚህን በምድር አቀፍ የወንድማማችነት ማህበር የተባበሩአቸውን ቅቡዓን ክርስቲያኖች ያገለግሉአቸዋል።—ማቴዎስ 25:34-40፤ 1 ጴጥሮስ 5:9
-