የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w03 2/15 ገጽ 31
  • የአንባብያን ጥያቄዎች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የአንባብያን ጥያቄዎች
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2003
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የይሖዋን ቃል በየዕለቱ መርምሩ!
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2000
  • ይሖዋ በደስታ እንድንጸና የሚረዳን እንዴት ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2022
  • ታማኙ መጋቢ፣ ዝግጁ ሆነህ ጠብቅ!
    ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
  • የማይታየውን እንደሚታይ አድርጋችሁ ጽኑ!
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2001
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2003
w03 2/15 ገጽ 31

የአንባብያን ጥያቄዎች

ኢሳይያስ 30:20 “ዓይኖችህ ግን አስተማሪህን ያያሉ” በማለት ይሖዋ ከፊታችን እንዳለ እየተናገረ ቁጥር 21 የይሖዋ ቃል ‘ከበስተኋላ’ እንደሚመጣ አድርጎ የሚናገረው ለምንድን ነው?

ኢሳይያስ 30:20, 21 እንዲህ ይላል:- “አስተማሪህ እንግዲህ ከአንተ አይሰወርም፤ ዓይኖችህ ግን አስተማሪህን ያያሉ፣ ወደ ቀኝም ወደ ግራም ፈቀቅ ብትል ጆሮችህ በኋላህ:- መንገዱ ይህች ናት በእርስዋም ሂድ የሚለውን ቃል ይሰማሉ።”

ጥቅሱን ቃል በቃል ከተረዳነው አንባቢው ታላቁን አስተማሪ ይሖዋን ከፊት ለፊቱ እያየው ድምፁን የሚሰማው ግን ከበስተኋላው ነው። ይሁን እንጂ ቃላቱ ምሳሌያዊ ስለሆኑ ልንረዳቸው የሚገባንም በዚያ መንገድ ነው።

አንድ ሰው ቁጥር 20ን ሲያነብብ ወደ አእምሮው የሚመጣው የጌታውን ትእዛዝ ተቀብሎ ለመፈጸም ዝግጁ የሆነን አገልጋይ ነው። አንድ አገልጋይ የጌታውን መመሪያ ለመረዳት እጁ የሚያመለክትበትን አቅጣጫ በትኩረት እንደሚከታተል ሁሉ በዛሬው ጊዜም የይሖዋ ሕዝቦች ይሖዋ በምድራዊ ድርጅቱ በኩል በየጊዜው የሚሰጣቸውን በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተመሠረቱ መመሪያዎች በንቃት ይከታተላሉ። (መዝሙር 123:1, 2) አዎን፣ ይሖዋ ‘በታማኝና ልባም ባሪያ’ በኩል የሚሰጣቸውን ማንኛውንም መመሪያ በትኩረት በመከታተል ፈቃዱን ይፈጽማሉ።​—⁠ማቴዎስ 24:45-47

ታዲያ አገልጋዮቹ ከበስተኋላቸው እንደሚሰሙት ተደርጎ የተገለጸው ድምፅ ምን ያመለክታል? ከበስተኋላ የሚሰሙት ድምፅ አምላክ በጥንት ጊዜ የተናገረውና ‘በታማኝ መጋቢው’ በኩል የሚብራራው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሰፈረው ቃሉ ነው ብሎ መደምደሙ ምክንያታዊ ይመስላል። (ሉቃስ 12:42) በጊዜያችን ያሉት የአምላክ አገልጋዮች ‘በታማኝና ልባም ባሪያ’ ማለትም ‘በታማኝ መጋቢው’ ተዘጋጅተው በሚቀርቡላቸው ጽሑፎች እየታገዙ መጽሐፍ ቅዱስን በትጋት በማጥናትና በውስጡ የሰፈሩትን መሠረታዊ መመሪያዎች በሥራ ላይ በማዋል የአምላክን ድምፅ ይሰማሉ። ታላቁ አስተማሪ ወቅቱን ጠብቆ በሚሰጣቸው መመሪያ ላይ በመታመንና መመሪያውን በሚገባ በማስተዋል እንዲሁም ከብዙ መቶ ዘመናት በፊት የተጻፈውን ቃሉን በማጥናት በምሳሌያዊ ሁኔታ ከፊት ለፊታቸው እያዩት ድምፁን ከኋላቸው ይሰሙታል።​—⁠ሮሜ 15:4

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ