-
“ጅረቱ በሚፈስበት ቦታ ያለው ነገር ሁሉ በሕይወት ይኖራል”የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
-
-
2 ሕዝቅኤል ወንዙ ወደ ሙት ባሕር እንደሚፈስ ተገነዘበ፤ የወንዙ ውኃ በደረሰበት ቦታ ሁሉ በሙት ባሕር ውስጥ ያለውን ሕይወት አልባና ጨዋማ የሆነ ውኃ በመፈወስ በዓሣዎች እንዲሞላ ያደርጋል። በወንዙ ዳርና ዳር ደግሞ ብዙ ዓይነት ዛፎች ይበቅላሉ። ዛፎቹ ለመብል የሚሆን አዲስ ፍሬ በየወሩ ይሰጣሉ፤ ቅጠላቸውም ለመድኃኒት ይሆናል። ሕዝቅኤል ይህን ሁሉ ሲመለከት ልቡ በሰላምና በተስፋ ተሞልቶ መሆን አለበት። ይሁን እንጂ ይህ የራእዩ ገጽታ ለእሱና በግዞት ላይ ላሉ ወገኖቹ ምን መልእክት ይዟል? በዛሬው ጊዜ ለምንኖረው ለእኛስ ምን መልእክት ያስተላልፋል?
-
-
“ጅረቱ በሚፈስበት ቦታ ያለው ነገር ሁሉ በሕይወት ይኖራል”የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
-
-
6. (ሀ) ራእዩ ምን አጽናኝ ተስፋ ይዟል? (ለ) ራእዩ ምን ማስጠንቀቂያ ያስተላልፋል? (የግርጌ ማስታወሻውን ተመልከት።)
6 ሕይወት ሰጪ ውኃ። በሕዝቅኤል ራእይ ላይ ወንዙ ወደ ሙት ባሕር ገብቶ አብዛኛውን የባሕሩን ክፍል እንደፈወሰው ተገልጿል። የሙት ባሕር ውኃ ተፈውሶ እንደ ታላቁ ባሕር ማለትም እንደ ሜድትራንያን ባሕር ብዙ ዓይነት ዓሣዎች የሚርመሰመሱበት ሆኗል። እንዲያውም በሙት ባሕር ዳርቻ “ከኤንገዲ እስከ ኤንዔግላይም ድረስ” ብዙዎች ዓሣ በማጥመድ ሥራ ተሰማርተዋል፤ እነዚህ ከተሞች ተራርቀው የሚገኙ ከተሞች ሳይሆኑ አይቀሩም። መልአኩ “ጅረቱ በሚፈስበት ቦታ ያለው ነገር ሁሉ በሕይወት ይኖራል” ብሏል። ይህ ሲባል ታዲያ ከይሖዋ ቤት የወጣው ወንዝ ሙት ባሕርን ሙሉ በሙሉ ያዳርሳል ማለት ነው? አይደለም። መልአኩ ሕይወት ሰጪ የሆነው ውኃ የማይደርስባቸው ረግረጋማ የሆኑ አንዳንድ ቦታዎች እንዳሉ ገልጿል። እነዚህ ቦታዎች “ጨዋማ እንደሆኑ ይቀራሉ።”b (ሕዝ. 47:8-11) ራእዩ፣ ንጹሕ አምልኮ ሕዝቡን በመንፈሳዊ ሕያው እንዲሆኑና ጥሩ ሕይወት እንዲመሩ እንደሚያስችላቸው የሚገልጽ አጽናኝ ተስፋ ይዟል። ይሁን እንጂ ራእዩ የሚያስተላልፈው ማስጠንቀቂያም አለ፦ የይሖዋን በረከት የሚቀበሉትም ሆነ ፈውስ የሚያገኙት ሁሉም አይደሉም።
-
-
“ጅረቱ በሚፈስበት ቦታ ያለው ነገር ሁሉ በሕይወት ይኖራል”የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
-
-
6. (ሀ) ራእዩ ምን አጽናኝ ተስፋ ይዟል? (ለ) ራእዩ ምን ማስጠንቀቂያ ያስተላልፋል? (የግርጌ ማስታወሻውን ተመልከት።)
6 ሕይወት ሰጪ ውኃ። በሕዝቅኤል ራእይ ላይ ወንዙ ወደ ሙት ባሕር ገብቶ አብዛኛውን የባሕሩን ክፍል እንደፈወሰው ተገልጿል። የሙት ባሕር ውኃ ተፈውሶ እንደ ታላቁ ባሕር ማለትም እንደ ሜድትራንያን ባሕር ብዙ ዓይነት ዓሣዎች የሚርመሰመሱበት ሆኗል። እንዲያውም በሙት ባሕር ዳርቻ “ከኤንገዲ እስከ ኤንዔግላይም ድረስ” ብዙዎች ዓሣ በማጥመድ ሥራ ተሰማርተዋል፤ እነዚህ ከተሞች ተራርቀው የሚገኙ ከተሞች ሳይሆኑ አይቀሩም። መልአኩ “ጅረቱ በሚፈስበት ቦታ ያለው ነገር ሁሉ በሕይወት ይኖራል” ብሏል። ይህ ሲባል ታዲያ ከይሖዋ ቤት የወጣው ወንዝ ሙት ባሕርን ሙሉ በሙሉ ያዳርሳል ማለት ነው? አይደለም። መልአኩ ሕይወት ሰጪ የሆነው ውኃ የማይደርስባቸው ረግረጋማ የሆኑ አንዳንድ ቦታዎች እንዳሉ ገልጿል። እነዚህ ቦታዎች “ጨዋማ እንደሆኑ ይቀራሉ።”b (ሕዝ. 47:8-11) ራእዩ፣ ንጹሕ አምልኮ ሕዝቡን በመንፈሳዊ ሕያው እንዲሆኑና ጥሩ ሕይወት እንዲመሩ እንደሚያስችላቸው የሚገልጽ አጽናኝ ተስፋ ይዟል። ይሁን እንጂ ራእዩ የሚያስተላልፈው ማስጠንቀቂያም አለ፦ የይሖዋን በረከት የሚቀበሉትም ሆነ ፈውስ የሚያገኙት ሁሉም አይደሉም።
-
-
“ጅረቱ በሚፈስበት ቦታ ያለው ነገር ሁሉ በሕይወት ይኖራል”የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
-
-
a በተጨማሪም ግዞተኞቹ አይሁዳውያን ከትውልድ አገራቸው መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ አንጻር ይህ ወንዝ እውነተኛ ወንዝ እንዳልሆነ ሳይገነዘቡ አይቀሩም፤ ምክንያቱም ወንዙ የሚፈሰው በትልቅ ተራራ ላይ ከሚገኝ ቤተ መቅደስ ተነስቶ ነው፤ ይህ ቤተ መቅደስ ደግሞ በተጠቀሰው ቦታ ላይ አይገኝም። ከዚህም ሌላ ራእዩ፣ ወንዙ ምንም ነገር ሳያግደው በቀጥታ ወደ ሙት ባሕር እንደፈሰሰ የሚጠቁም ሊሆን ይችላል፤ ይህም ቢሆን ከአካባቢው መልክዓ ምድር አንጻር ሊሆን የሚችል ነገር አይደለም።
-