-
“ጅረቱ በሚፈስበት ቦታ ያለው ነገር ሁሉ በሕይወት ይኖራል”የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
-
-
2 ሕዝቅኤል ወንዙ ወደ ሙት ባሕር እንደሚፈስ ተገነዘበ፤ የወንዙ ውኃ በደረሰበት ቦታ ሁሉ በሙት ባሕር ውስጥ ያለውን ሕይወት አልባና ጨዋማ የሆነ ውኃ በመፈወስ በዓሣዎች እንዲሞላ ያደርጋል። በወንዙ ዳርና ዳር ደግሞ ብዙ ዓይነት ዛፎች ይበቅላሉ። ዛፎቹ ለመብል የሚሆን አዲስ ፍሬ በየወሩ ይሰጣሉ፤ ቅጠላቸውም ለመድኃኒት ይሆናል። ሕዝቅኤል ይህን ሁሉ ሲመለከት ልቡ በሰላምና በተስፋ ተሞልቶ መሆን አለበት። ይሁን እንጂ ይህ የራእዩ ገጽታ ለእሱና በግዞት ላይ ላሉ ወገኖቹ ምን መልእክት ይዟል? በዛሬው ጊዜ ለምንኖረው ለእኛስ ምን መልእክት ያስተላልፋል?
-
-
“ጅረቱ በሚፈስበት ቦታ ያለው ነገር ሁሉ በሕይወት ይኖራል”የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
-
-
6. (ሀ) ራእዩ ምን አጽናኝ ተስፋ ይዟል? (ለ) ራእዩ ምን ማስጠንቀቂያ ያስተላልፋል? (የግርጌ ማስታወሻውን ተመልከት።)
6 ሕይወት ሰጪ ውኃ። በሕዝቅኤል ራእይ ላይ ወንዙ ወደ ሙት ባሕር ገብቶ አብዛኛውን የባሕሩን ክፍል እንደፈወሰው ተገልጿል። የሙት ባሕር ውኃ ተፈውሶ እንደ ታላቁ ባሕር ማለትም እንደ ሜድትራንያን ባሕር ብዙ ዓይነት ዓሣዎች የሚርመሰመሱበት ሆኗል። እንዲያውም በሙት ባሕር ዳርቻ “ከኤንገዲ እስከ ኤንዔግላይም ድረስ” ብዙዎች ዓሣ በማጥመድ ሥራ ተሰማርተዋል፤ እነዚህ ከተሞች ተራርቀው የሚገኙ ከተሞች ሳይሆኑ አይቀሩም። መልአኩ “ጅረቱ በሚፈስበት ቦታ ያለው ነገር ሁሉ በሕይወት ይኖራል” ብሏል። ይህ ሲባል ታዲያ ከይሖዋ ቤት የወጣው ወንዝ ሙት ባሕርን ሙሉ በሙሉ ያዳርሳል ማለት ነው? አይደለም። መልአኩ ሕይወት ሰጪ የሆነው ውኃ የማይደርስባቸው ረግረጋማ የሆኑ አንዳንድ ቦታዎች እንዳሉ ገልጿል። እነዚህ ቦታዎች “ጨዋማ እንደሆኑ ይቀራሉ።”b (ሕዝ. 47:8-11) ራእዩ፣ ንጹሕ አምልኮ ሕዝቡን በመንፈሳዊ ሕያው እንዲሆኑና ጥሩ ሕይወት እንዲመሩ እንደሚያስችላቸው የሚገልጽ አጽናኝ ተስፋ ይዟል። ይሁን እንጂ ራእዩ የሚያስተላልፈው ማስጠንቀቂያም አለ፦ የይሖዋን በረከት የሚቀበሉትም ሆነ ፈውስ የሚያገኙት ሁሉም አይደሉም።
-
-
ቀስ እያለ የሚፈሰው ውኃ ትልቅ ወንዝ ሆነ!የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
-
-
ሕይወት ሰጪ ውኃ
በጥንት ዘመን፦ ይሖዋ ታዛዥ የሆኑ ሕዝቦቹን በመንፈሳዊ ሕያው እንዲሆኑና ጥሩ ሕይወት እንዲመሩ በማድረግ አብዝቶ ባርኳቸዋል
በዘመናችን፦ ከጊዜ ወደ ጊዜ ቁጥራቸው እየጨመረ የመጣ ሰዎች፣ በመንፈሳዊው ገነት ውስጥ በብዛት እየፈሰሰ ያለውን የይሖዋን በረከት ማግኘትና በመንፈሳዊ ሕያው መሆን ችለዋል
ወደፊት፦ በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ከሞት ተነስተው አርማጌዶንን በሕይወት ካለፉ ሰዎች ጋር በገነት ይኖራሉ፤ የይሖዋ በረከት ለሁሉም ተትረፍርፎ ይፈስላቸዋል
-
-
“ጅረቱ በሚፈስበት ቦታ ያለው ነገር ሁሉ በሕይወት ይኖራል”የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
-
-
12. (ሀ) የመጽሐፍ ቅዱስ እውነት ሰዎችን የጠቀማቸው እንዴት ነው? (ለ) ራእዩ ምን ማስጠንቀቂያ ይዞልናል? (የግርጌ ማስታወሻውንም ተመልከት።)
12 ሕይወት ሰጪ ውኃ። ሕዝቅኤል “ጅረቱ በሚፈስበት ቦታ ያለው ነገር ሁሉ በሕይወት” እንደሚኖር ተነግሮታል። የእውነት ውኃ ወደ መንፈሳዊው ገነት ለመጡ ሁሉ እንዴት እንደፈሰሰላቸው ለማሰብ ሞክር። የመጽሐፍ ቅዱስ እውነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ቅን ልብ ያላቸው ሰዎች በመንፈሳዊ ሁኔታ ሕያውና ጤናማ እንዲሆኑ አስችሏቸዋል። ይሁን እንጂ ራእዩ፣ ለዚህ እውነት ምላሽ መስጠታቸውን የሚቀጥሉት ሁሉም ሰዎች እንዳልሆኑ የሚያሳይ ማስጠንቀቂያም ይዟል። በሕዝቅኤል ራእይ ላይ በሙት ባሕር ውስጥ ወንዙ ያልፈወሳቸው ረግረጋማና ውኃ ያቆሩ ቦታዎች እንዳሉ ተገልጾ ነበር፤ ከዚህ ጋር በሚመሳሰል ሁኔታ አንዳንድ ሰዎች የሆነ ወቅት ላይ ልባቸው በመደንደኑ ለእውነት በጎ ምላሽ መስጠታቸውን አቁመዋል።c ይህ ሁኔታ ፈጽሞ እኛ ላይ እንዲደርስ አንፈልግም!—ዘዳግም 10:16-18ን አንብብ።
-