-
ከአንበሶች መንጋጋ ዳነ!የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
-
-
16. (ሀ) ዳርዮስ ለዳንኤል አምላክ አክብሮት የነበረው ለምንድን ነው? (ለ) ዳርዮስ ዳንኤልን በሚመለከት ምን ተስፋ ነበረው?
16 ዳርዮስ ምንም ማድረግ እንደማይችል ተገነዘበ። ሕጉ ሊሻርም ሆነ የዳንኤል “በደል” ሊደመሰስ አይችልም። ዳርዮስ “ሁልጊዜ የምታመልከው [“ሳታወላውል የምታገለግለው፣” NW] አምላክህ እርሱ ያድንህ” ከማለት ሌላ ምንም ሊያደርግ አልቻለም። ዳርዮስ ለዳንኤል አምላክ አክብሮት የነበረው ይመስላል። ዳንኤል ስለ ባቢሎን ውድቀት ትንቢት እንዲናገር ያስቻለው ይሖዋ ነው። ከሌሎቹ የመንግሥቱ ባለ ሥልጣናት ሁሉ ለየት ብሎ እንዲታይ ያደረገውን “የላቀ መንፈስ የሰጠውም” አምላክ ነው። ምናልባትም ዳርዮስ ከብዙ አሥርተ ዓመታት በፊት ይኸው አምላክ ሦስቱን ወጣት ዕብራውያን ከእሳት እቶን ውስጥ እንዳወጣቸው ሳይሰማ አይቀርም። ዳርዮስ በፊርማው ያጸደቀውን ትእዛዝ መሻር ስላልቻለ አሁንም ይሖዋ ዳንኤልን ሊያድነው እንደሚችል ተስፋ ሳያደርግ አልቀረም። ከዚህ በኋላ ዳንኤል ወደ አንበሶቹ ጉድጓድ ተጣለ።c “ድንጋይም አምጥተው በጉድጓዱ አፍ ላይ ገጠሙበት፤ ንጉሡም በዳንኤል ላይ የተደረገው እንዳይለወጥ በቀለበቱና በመኳንንቱ ቀለበት አተመው።”—ዳንኤል 6:16, 17
-
-
ከአንበሶች መንጋጋ ዳነ!የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
-
-
c የአንበሶቹ ጉድጓድ ከላይ አፍ ያለው የምድር ውስጥ ቤት ሊሆን ይችላል። ከዚህም በተጨማሪ ለእንስሶቹ መግቢያ የሚሆን በር ወይም ተከፋች እንደነበረው እሙን ነው።
-