-
ከአንበሶች መንጋጋ ዳነ!የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
-
-
20. ተንኮለኞቹ የዳንኤል ጠላቶች መጨረሻቸው ምን ሆነ?
20 ዳንኤል ደህና መሆኑ ከተረጋገጠ በኋላ ዳርዮስ የሚጨርሰው ሌላ ጉዳይ ነበረው። “ንጉሡም አዘዘ፣ ዳንኤልንም የከሰሱ እነዚያን ሰዎች አመጡአቸው፣ እነርሱንና ልጆቻቸውንም ሚስቶቻቸውንም በአንበሶች ጉድጓድ ጣሉአቸው፤ ወደ ጉድጓዱም መጨረሻ ሳይደርሱ አንበሶች ያዙአቸው አጥንታቸውንም ሁሉ ሰባበሩ።”d—ዳንኤል 6:24
21. ኃጢአት የፈጸሙ የቤተሰብ አባላትን በሚመለከት በሙሴ ሕግና በጥንት ባሕሎች ሕግ መካከል ምን ልዩነት ነበር?
21 ያሴሩትን ሰዎች ብቻ ሳይሆን ሚስቶቻቸውንና ልጆቻቸውን ጨምሮ ማስገደሉ ምክንያታዊነት የጎደለው ጭካኔ ሊመስል ይችላል። ከዚህ በተቃራኒ አምላክ ለሙሴ የሰጠው ሕግ “አባቶች ስለ ልጆች አይገደሉ፣ ልጆችም ስለ አባቶች አይገደሉ፤ ነገር ግን ሁሉ እያንዳንዱ በኃጢአቱ ይገደል” ይላል። (ዘዳግም 24:16) ሆኖም በአንዳንድ የጥንት ባሕሎች ውስጥ ከባድ ወንጀል በሚፈጸምበት ጊዜ ከበደለኛው ሰው ጋር የቤተሰቡን አባላት ጨምሮ መግደል እንግዳ ነገር አልነበረም። ይህም የሚደረገው የቤተሰቡ አባላት የኋላ ኋላ የበቀል እርምጃ ለመውሰድ እንዳይነሳሱ ሊሆን ይችላል። ያም ሆነ ይህ በመንግሥቱ አለቆችና በመሳፍንቱ ቤተሰቦች ላይ በተወሰደው በዚህ እርምጃ የዳንኤል እጅ እንደሌለበት ግልጽ ነው። እነዚህ ክፉ ሰዎች በቤተሰቦቻቸው ላይ ባመጡት መከራ እጅግ እንዳዘነ ምንም ጥርጥር የለውም።
-
-
ከአንበሶች መንጋጋ ዳነ!የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
-
-
d ‘መክሰስ’ የሚለው ቃል “ስም ማጥፋት” ተብሎም ሊተረጎም ከሚችል የአረማይክ አገላለጽ የተተረጎመ ነው። ይህም የዳንኤል ጠላቶች የነበራቸውን ተንኮል ያዘለ ሐሳብ የሚያጎላ ነው።
-