-
ከአምላክ ዘንድ የመጣ መልእክተኛ አበረታውየዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
-
-
9, 10. (ሀ) ዳንኤል ራእዩ ሲመጣለት የት ነበር? (ለ) ዳንኤል በራእይ ያየው ነገር ምን እንደሆነ ግለጽ።
9 ዳንኤል በተስፋ መቁረጥ አልተዋጠም። ቀጥሎ ስለሆነው ነገር እንዲህ በማለት ይነግረናል:- “ጤግሮስ [“ሂዴኬል፣” NW] በተባለው በታላቁ ወንዝ አጠገብ ሳለሁ፣ ዓይኔን አነሣሁ፣ እነሆም፣ በፍታ የለበሰውን ጥሩም የአፌዝን ወርቅ በወገቡ ላይ የታጠቀውን ሰው አየሁ።” (ዳንኤል 10:4, 5) ሂዴኬል ከኤደን ገነት ይወጡ ከነበሩት አራት ወንዞች መካከል አንዱ ነው። (ዘፍጥረት 2:10-14) በጥንቷ ፋርስ ሂዴኬል የሚታወቀው ጤግራ በመባል ሲሆን ጤግሮስ ከሚለው የግሪክኛ ስም የተገኘ ነው። በሂዴኬልና በኤፍራጥስ ወንዝ መካከል ያለው ቦታ መሶጴጣሚያ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ትርጉሙም “በሁለት ወንዞች መካከል ያለ ቦታ” ማለት ነው። ይህም ዳንኤል ራእዩን ሲቀበል በባቢሎን ከተማ ላይሆን ቢችልም በባቢሎንያ ምድር እንደነበር ያረጋግጣል።
-
-
ከአምላክ ዘንድ የመጣ መልእክተኛ አበረታውየዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
-
-
12, 13. የመልእክተኛው (ሀ) ልብስ (ለ) ሰውነት ምን ይጠቁማል?
12 እስቲ ዳንኤልን ይህን ያህል ስላስፈራው ባለ ግርማ መልእክተኛ በጥልቀት እንመርምር። ‘በፍታ ለብሶ ወገቡን በጥሩ የአፌዝ ወርቅ ታጥቋል።’ በጥንቷ እስራኤል የነበረው ሊቀ ካህናት መታጠቂያው፣ ኤፉዱና የደረት ኪሱ እንዲሁም የቀሩት ካህናት የሚለብሱት ልብስ የሚዘጋጀው በብልሃት ከተሠራ በፍታ ሲሆን በወርቅ ይጌጥ ነበር። (ዘጸአት 28:4-8፤ 39:27-29) በመሆኑም የመልእክተኛው ልብስ ቅድስናንና የሥልጣን ክብር የሚያሳይ ነው።
13 ዳንኤል በመልክተኛውም ሰውነት ማለትም እንደ ከበረ ማዕድን ባለው የሰውነቱ አንጸባራቂ ክብር፣ ዓይን የሚያጥበረብረው የፊቱ ነፀብራቅ፣ እንደ ጦር በሚዋጉት ዓይኖቹና በሚያንጸባርቁት ፈርጣማ እጅና እግሮቹ በፍርሃት ተውጦ ነበር። ሌላው ቀርቶ እንደ ነጎድጓድ የሚያስገመግመው ድምፁም ራሱ አስፈሪ ነበር። ይህ ሁሉ ነገር ከሰው በላይ የሆነ ኃይል እንዳለው የሚያሳይ ነበር። ይህ ‘የበፍታ ልብስ የለበሰ ሰው’ በይሖዋ ፊት የሚያገለግል ከፍተኛ ሥልጣን ያለው መልአክ እንጂ ሌላ ሊሆን አይችልም። መልእክቱንም ያመጣው ከይሖዋ ነው።a
-
-
ከአምላክ ዘንድ የመጣ መልእክተኛ አበረታውየዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
-
-
a ይህ መልአክ በስም ባይጠቀስም ስላየው ራእይ ዳንኤልን ይረዳው ዘንድ ለገብርኤል መመሪያ ሲሰጥ ድምፁ የተሰማው መልአክ ይመስላል። (ዳንኤል 8:2, 15, 16ን ከዳን 12:7, 8 ጋር አወዳድር።) ከዚህም በተጨማሪ ዳንኤል 10:13 ‘ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ’ የሆነው ሚካኤል ይህንን መልአክ ሊረዳው እንደመጣ ይገልጻል። በመሆኑም ይህ ስሙ ያልተገለጸው መልአክ ከገብርኤልና ከሚካኤል ጋር በቅርብ የመሥራት መብት ያለው መልአክ መሆን ይኖርበታል።
-