-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 27—ዳንኤል“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 15
-
-
20 ዳንኤል የተመለከታቸውን ራእዮች መከለሳችን የሚያስደስትና እምነት የሚያጠነክር ነው። እስቲ በመጀመሪያ የዓለም ኃያል መንግሥታትን በተመለከተ ያያቸውን አራት ራእዮች እንመልከት:- (1) የመጀመሪያው ስለ አንድ አስፈሪ ምስል የሚገልጸው ራእይ ነበር፤ ከወርቅ የተሠራው የዚህ ምስል ራስ ከናቡከደናፆር ጀምሮ ያሉትን የባቢሎን ነገሥታት ሥርወ መንግሥት የሚያመለክት ሲሆን ቀሪዎቹ የምስሉ አካሎች ደግሞ ከእነዚህ ነገሥታት በኋላ የሚነሱ ሌሎች ሦስት መንግሥታትን ያመለክታሉ። አንድ “ድንጋይ” እነዚህን መንግሥታት ካደቀቃቸው በኋላ “ፈጽሞ የማይፈርስ . . . መንግሥት” ሆነ፤ ይህም የአምላክ መንግሥት ነው። (2:31-45) (2) ከዚያ በኋላ ዳንኤል ራሱ የተመለከታቸው ራእዮች ተገልጸዋል፤ ከእነዚህ ውስጥ የመጀመሪያው፣ አራት ‘መንግሥታትን’ ስለሚወክሉት አራት አራዊት የሚናገረው ራእይ ነው። አራዊቱ አንበሳ፣ ድብና አራት ራስ ያለው ነብር የሚመስሉ እንዲሁም ትላልቅ የብረት ጥርስና አሥር ቀንድ ያለው በኋላም አንድ ትንሽ ቀንድ ያበቀለ አውሬ ናቸው። (7:1-8, 17-28) (3) ቀጥሎ ደግሞ የአውራው በግ (ሜዶ ፋርስ)፣ የአውራው ፍየል (ግሪክ) እና የአንድ ትንሽ ቀንድ ራእይ ተገልጿል። (8:1-27) (4) በመጨረሻም የደቡቡን ንጉሥና የሰሜኑን ንጉሥ ራእይ እናገኛለን። ዳንኤል 11:5-19 እስክንድር በ323 ከክርስቶስ ልደት በፊት ሲሞት በግሪክ ግዛት ውስጥ በተነሡት የግብፅና የሴሉሲድ ነገሥታት መካከል የነበረውን ግጭት በትክክል ይገልጻል። ትንቢቱ ከቁጥር 20 አንሥቶ በደቡቡ ንጉሥና በሰሜኑ ንጉሥ ቦታ ስለሚነሱት ብሔራት መዘርዘሩን ይቀጥላል። ኢየሱስ የእርሱን መገኘት ስለሚጠቁሙት ምልክቶች በተናገረው ትንቢት ውስጥ ‘ጥፋትን ስለሚያመጣው የጥፋት ርኩሰት’ (11:31) መግለጹ በእነዚህ ሁለት ነገሥታት መካከል የሚደረገው የሥልጣን ሽኩቻ እስከ ‘ዓለም መጨረሻ’ ድረስ እንደሚዘልቅ ያሳያል። (ማቴ. 24:3) “መንግሥታት ከተመሠረቱበት ጊዜ ጀምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ ታይቶ የማይታወቅ ታላቅ የመከራ ጊዜ” በሚሆንበት በዚያ ወቅት ለአምላክ አክብሮት የሌላቸውን ብሔራት ለማጥፋትና ታዛዥ ለሆኑት የሰው ልጆች ሰላምን ለማምጣት ሚካኤል ራሱ እንደሚነሣ ይህ ትንቢት የሚሰጠው ማረጋገጫ እንዴት የሚያጽናና ነው!—ዳን. 11:20 እስከ 12:1
-
-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 27—ዳንኤል“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 15
-
-
23 የአምላክ መንግሥት ተስፋ በዳንኤል መጽሐፍ ውስጥ እምነትን በሚያጎለብት መንገድ ጎላ ተደርጎ ተገልጿል! ይሖዋ አምላክ፣ ፈጽሞ የማይፈርስና ሌሎች መንግሥታትን ሁሉ የሚያደቅቅ መንግሥት የሚያቋቁም ሉዓላዊ ገዥ መሆኑ ተገልጿል። (2:19-23, 44፤ 4:25) አረማዊ የነበሩት ንጉሥ ናቡከደነፆርና ንጉሥ ዳርዮስ እንኳ የይሖዋን የበላይነት አምነው ለመቀበል ተገደዋል። (3:28, 29፤ 4:2, 3, 37፤ 6:25-27) ይሖዋ በመንግሥቱ ላይ ለተነሣው አከራካሪ ጉዳይ እልባት በማበጀት ‘የሰውን ልጅ ለሚመስለው’ የዘላለም ‘ሥልጣን፣ ክብርና ታላቅ ኀይል እንደሚሰጠውና በልዩ ልዩ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች፣ መንግሥታትና ሕዝቦች እንዲሰግዱለት’ እንደሚያደርግ በዘመናት የሸመገለ ንጉሥ ተደርጎ ተወድሷል እንዲሁም ክብር ተሰጥቶታል። “የሰው ልጅ” ተብሎ ከተገለጸው ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር በመንግሥቱ የሚካፈሉት “የልዑሉ ቅዱሳን” ናቸው። (ዳን. 7:13, 14, 18, 22፤ ማቴ. 24:30፤ ራእይ 14:14) በመንግሥት ሥልጣኑ ተጠቅሞ የዚህን አሮጌ ዓለም መንግሥታት ሁሉ የሚያደቅቀውና የሚያጠፋው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ነው። (ዳን. 12:1፤ 2:44፤ ማቴ. 24:3, 21፤ ራእይ 12:7-10) ጽድቅ ወዳድ የሆኑ ሰዎች እነዚህን ትንቢቶችና ራእዮች መረዳታቸው፣ ንቁ እንዲሆኑ እንዲሁም በመንፈስ አነሳሽነት በተጻፈውና ጠቃሚ በሆነው የዳንኤል መጽሐፍ አማካኝነት የተገለጡልንን ስለ አምላክ መንግሥት ዓላማዎች የሚገልጹትን እውነተኛዎቹን “አስደናቂ ነገሮች” ለማወቅ የአምላክን ቃል እንዲመረምሩ ሊያነሳሳቸው ይገባል።—ዳን. 12:2, 3, 6
-