-
‘በምድራችን’ ላይ የወረደው የይሖዋ በረከትመጠበቂያ ግንብ—1999 | መጋቢት 1
-
-
4, 5. በኢዩኤል ትንቢት ላይ የተገለጸው ወንዝ በሕዝቅኤል ላይ ከተገለጸው ጋር የሚመሳሰለው እንዴት ነው?
4 ይህ አስደሳች ትንቢት ግዞተኞቹ አይሁዳውያን ከሁለት መቶ ዓመታት በፊት የተነገረ ሌላ ትንቢት እንዲያስታውሱ ሳያደርጋቸው አልቀረም። “ከእግዚአብሔርም ቤት ምንጭ ትፈልቃለች፣ የሰጢምንም ሸለቆ ታጠጣለች።”a (ኢዩኤል 3:18) የኢዩኤል ትንቢትም እንደ ሕዝቅኤል ትንቢት ከቤተ መቅደሱ ማለትም ከአምላክ ቤት ወንዝ እንደሚመነጭና በረሐ የሆነ አካባቢ እንደሚያለመልም ይተነብያል።
5 የኢዩኤል ትንቢት በዚህ በዘመናችን በመፈጸም ላይ እንደሚገኝ መጠበቂያ ግንብ ሲገልጽ ቆይቷል።b ከዚህ ጋር ተመሳሳይ የሆነው የሕዝቅኤል ትንቢትም የተለየ አይሆንም። ዛሬም ዳግመኛ በተቋቋመው የአምላክ ሕዝቦች ምድር እንደ ጥንቱ የእስራኤል ምድር የይሖዋ በረከቶች ፈስሰዋል።
-
-
‘በምድራችን’ ላይ የወረደው የይሖዋ በረከትመጠበቂያ ግንብ—1999 | መጋቢት 1
-
-
a ይህ የሰጢም ሸለቆ ከኢየሩሳሌም በስተ ደቡብ ምሥራቅ ተነስቶ ወደ ሙት ባሕር የሚገባውን የቄድሮን ሸለቆ ሳያመለክት አይቀርም። በተለይ ዝቅተኛ ቦታው ውኃ አልባና ዓመቱን ሙሉ ደረቅ ነው።
-