-
የመጽሐፍ ቅዱስ ተቺዎችን ያሳፈረው ጠፍቶ የነበረው መንግሥትመጠበቂያ ግንብ—1993 | ሰኔ 1
-
-
የግሪክ ታሪክ ጸሐፊ የሆነው ዲዮዶረስ ሲኩለስ ይኖር የነበረው ከ2000 ዓመታት በፊት ነበር። ዲዮዶረስ የጠቀሳት ነነዌ አራት ማእዘን የሆነች ከተማ ነበረች። የአራቱም ጎኖቿ ጠቅላላ ርዝመት 480 ስታዲያ ነው። ይህም ማለት ጠቅላላ ዙሪያዋ 96 ኪሎ ሜትር ነው! መጽሐፍ ቅዱስም ነነዌ “የሦስት ቀን መንገድ ያህል እጅግ ታላቅ ከተማ” እንደሆነች በመጥቀስ ተመሳሳይ መግለጫ ይሰጣል። — ዮናስ 3:3
የ19ኛው መቶ ዘመን የመጽሐፍ ቅዱስ ተቺዎች ግን አንዲት የማትታወቅ በጥንቱ ዓለም የነበረች ከተማ ይህን ያህል ሰፊ ልትሆን ትችላለች ብለው ለማመን አሻፈረኝ ብለው ነበር። በተጨማሪም እነዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ተቺዎች ነነዌ በዚያን ጊዜ የነበረች ከሆነ ከባቢሎን በፊት የነበረው ስልጣኔ ክፍል መሆን አለባት ብለው ነበር።
-
-
የመጽሐፍ ቅዱስ ተቺዎችን ያሳፈረው ጠፍቶ የነበረው መንግሥትመጠበቂያ ግንብ—1993 | ሰኔ 1
-
-
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሌላው በቁፋሮ የጥንት ታሪክ ተመራማሪ የሆኑት አውስቲን ሄነሪ ሌያርድ ከኮርሳባድ ደቡባዊ ምዕራብ 42 ኪሎ ሜትር ገደማ ርቆ በሚገኝ ኒምሩድ ተብሎ በሚጠራ ቦታ ላይ ያለውን ፍርስራሽ መቆፈር ጀመሩ። ፍርስራሹም በዘፍጥረት 10:11 ላይ ተጠቅሰው ከነበሩት አራት ከተሞች ውስጥ የአንዱ የካለህ መሆኑ ተረጋገጠ። ከዚያም ሌያርድ በ1849 በካለህና በኮርሳባድ መካከል ኩዩንጂክ ተብሎ በሚጠራ ቦታ ላይ የሚገኝ የአንድ ትልቅ ቤተ መንግሥት ፍርስራሽ ቆፍረው አወጡ። ቤተ መንግሥቱ የነነዌ ክፍል እንደነበረ ተረጋገጠ። በኮርሳባድና በካለህ መካከል ካራምለስ ተብሎ የሚጠራውን ጉብታ ጨምሮ የሌሎች መንደሮች ፍርስራሾችም ይገኛሉ። “የኒምሩድን [ካለህን] የኩዩንጂክን [ነነዌን]፣ የኮርሳባድን እንዲሁም የካራምለስን አራት ትልልቅ ጉብታዎች የከተማይቱ አራት ጎን ማዕዘኖች አድርገን ከወሰድን የከተማዋ ስፋት የመልከዓ ምድር አጥኚው ካስቀመጠው 480 ስታዲያ ወይም 96 ኪሎ ሜትር ርዝመት እንዲሁም ከነቢዩ [ዮናስ] የሦስት ቀን መንገድ ጋር በትክክል የሚስማማ ሆኖ እናገኘዋለን።”
እንግዲያው ዮናስ እነዚህን መንደሮች በዘፍጥረት 10:11 ላይ ነነዌ በመባል መጀመሪያ በተመዘገበችው ከተማ ስም “ታላቅ ከተማ” ብሎ በመጥራት በአንድ ላይ እንዳጠቃለላቸው ግልጽ ነው። በዘመናችንም ተመሳሳይ ነገር ይደረጋል። ለምሳሌ ያህል መጀመሪያ በነበረችው ለንደንና አሁን በዳር ባሉት ከተማዎች መካከል ልዩነት አለ። እንዲያውም እነዚህ ከተማዎች በመኖራቸው አንዳንድ ጊዜ “ታላቋ ለንደን” ተብላ እንድትጠራ አድርገዋታል።
-