-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 33—ሚክያስ“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 15
-
-
6 በሚክያስ 5:2 ላይ መሲሑ ስለሚወለድበት ቦታ የሚናገረው ጎላ ብሎ የሚታይ ትንቢት የሚክያስ መጽሐፍ በመንፈስ አነሳሽነት የተጻፈ ስለመሆኑ የሚነሳውን ጥርጥር ሙሉ በሙሉ ያስወግዳል። (ማቴ. 2:4-6) በተጨማሪም በክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ ከሚክያስ መጽሐፍ ጋር የሚመሳሰሉ ሐሳቦች አሉ።—ሚክ. 7:6, 20፤ ማቴ. 10:35, 36፤ ሉቃስ 1:72, 73
-
-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 33—ሚክያስ“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 15
-
-
18 በሚክያስ ትንቢት መሠረት ኢየሱስ በቤተ ልሔም መወለዱ መጽሐፉ በአምላክ መንፈስ የተጻፈ መሆኑን ከማረጋገጡ በተጨማሪ በዚህ ቁጥር ዙሪያ የተገለጹት ሐሳቦች በክርስቶስ ኢየሱስ በሚተዳደረው የአምላክ መንግሥት ግዛት ሥር የሚኖረውን ሁኔታ የሚተነብዩ መሆናቸውን ያመለክታል። ከቤተ ልሔም (የዳቦ ቤት ማለት ነው) የሚወጣውና በመሥዋዕቱ ለሚያምኑ ሁሉ የዘላለም ሕይወት የሚያስገኘው ኢየሱስ ነው። “በእግዚአብሔር ኀይል . . . መንጋውንም ይጠብቃል” የተባለለትና ዳግመኛ በሚቋቋመውና አንድ በሚሆነው የአምላክ መንጋ መካከል እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ታላቅ በመሆን ሰላም እንዲመሠረት የሚያደርገው እርሱ ነው።—ሚክ. 5:2, 4፤ 2:12፤ ዮሐ. 6:33-40
-