የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ምክንያታዊነትን አዳብር
    መጠበቂያ ግንብ—1994 | ነሐሴ 1
    • ሁኔታዎች ሲለወጡ እርምጃንም አብሮ ማስተካከል

      6. ኢየሱስ ልጅዋን የአጋንንት መንፈስ የተጠናወተባትን ሴት ባነጋገረ ጊዜ ምክንያታዊነትን ያሳየው እንዴት ነው?

      6 ኢየሱስ ልክ እንደ ይሖዋ አዳዲስ ሁኔታዎች ሲከሰቱ ወዲያውኑ ሊወስድ ያሰበውን እርምጃ እንደሚለውጥ ወይም ክስተቶቹን እንደ ሁኔታው እንደሚያስተናግድ አስመስክሯል። በአንድ ወቅት አንዲት ከአሕዛብ ወገን የሆነች ሴት የአጋንንት መንፈስ ክፉኛ የተጠናወታትን ልጅዋን እንዲፈውስላት ተማጸነችው። በመጀመሪያ በሦስት የተለያዩ መንገዶች በመጠቀም ይኸውም አንደኛ ላቀረበችው ጥያቄ መልስ ከመስጠት በመታቀብ፤ ሁለተኛ ወደ ምድር የተላከው ለአሕዛብ ሳይሆን ለአይሁዶች እንደሆነ በቀጥታ በመግለጽና ሦስተኛ ደግሞ ይህንኑ ነጥብ በደግነት የሚያስገነዝብ ምሳሌ በመናገር ሊረዳት እንደማይችል ነገራት። ሴትየዋ ግን ይህን ሁሉ በመቋቋም ከፍተኛ እምነት እንዳላት አሳየች። ኢየሱስ ይህን ያልተለመደ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት ይህ ወቅት አጠቃላይ የሆነ ደንብ የሚተገበርበት ጊዜ ሳይሆን ታላላቅ ለሆኑ መሠረታዊ ሥርዓቶች ምላሽ በመስጠት እርምጃን ማስተካከል የሚያስፈልግበት ጊዜ መሆኑን ተረዳ።a ስለዚህ ኢየሱስ ሦስት ጊዜ አላደርገውም ብሎ የጠቆመውን ነገር አደረገ። የሴቲቱን ልጅ ፈወሳት!—ማቴዎስ 15:21–28

  • ምክንያታዊነትን አዳብር
    መጠበቂያ ግንብ—1994 | ነሐሴ 1
    • [በገጽ 16 ላይ የሚገኝ ሥዕል]

      አንዲት ሴት ከፍተኛ እምነት ባሳየች ጊዜ ኢየሱስ አጠቃላይ የሆነ ደንብ የሚከተልበት ወቅት እንዳልሆነ ተረድቶ ነበር

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ