የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ይሖዋና ኢየሱስ አንድ እንደሆኑ ሁላችንም አንድ እንሁን
    መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2018 | ሰኔ
    • ፍቅርና ትሕትና በማዳበር ጭፍን ጥላቻን ማሸነፍ

      8. በክርስቲያኖች መካከል ላለው አንድነት በጣም አስፈላጊ የሆነው መሠረታዊ እውነታ ምንድን ነው? አብራራ።

      8 ኢየሱስ ለአንድነታችን በጣም አስፈላጊ የሆነውን መሠረታዊ እውነታ ለተከታዮቹ ሲናገር “ሁላችሁም ወንድማማቾች ናችሁ” ብሏቸዋል። (ማቴዎስ 23:8, 9⁠ን አንብብ።) “ወንድማማቾች” እንድንባል የሚያደርገን አንዱ ምክንያት ሁላችንም የአዳም ልጆች መሆናችን ነው። (ሥራ 17:26) ምክንያቱ ግን ይህ ብቻ አይደለም። የኢየሱስ ተከታዮች፣ ይሖዋን እንደ ሰማያዊ አባታቸው አድርገው ስለሚቀበሉ ሁሉም ወንድማማችና እህትማማች እንደሆኑ ኢየሱስ ገልጿል። (ማቴ. 12:50) በተጨማሪም የክርስቶስ ተከታዮች በፍቅርና በእምነት የተሳሰረ የአንድ ትልቅ መንፈሳዊ ቤተሰብ አባላት ናቸው። ሐዋርያት በጻፏቸው ደብዳቤዎች ላይ የእምነት ባልንጀሮቻቸውን ‘ወንድሞች’ እና ‘እህቶች’ ብለው የጠሯቸው ለዚህ ነው።—ሮም 1:13፤ 1 ጴጥ. 2:17፤ 1 ዮሐ. 3:13a

  • ይሖዋና ኢየሱስ አንድ እንደሆኑ ሁላችንም አንድ እንሁን
    መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2018 | ሰኔ
    • a “ወንድሞች” የሚለው አጠራር በጉባኤ ውስጥ ያሉ ሴቶችንም ይጨምራል። ጳውሎስ ደብዳቤውን የጻፈው በሮም ለሚገኙ “ወንድሞች” ቢሆንም ይህን ያለው እህቶችንም በአእምሮው ይዞ ነው። በደብዳቤው ላይ አንዳንድ እህቶችን በስም መጥቀሱ ይህን ያሳያል። (ሮም 16:3, 6, 12) ቀደም ካሉት ዘመናት ጀምሮ መጠበቂያ ግንብ መጽሔት በጉባኤ ውስጥ ያሉ ክርስቲያኖችን ለመግለጽ ‘ወንድሞችና እህቶች’ የሚለውን አጠራር ሲጠቀም ቆይቷል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ