-
ለይሖዋ ቀን ተዘጋጅታችኋል?መጠበቂያ ግንብ—1997 | መጋቢት 1
-
-
9. በማቴዎስ 24:36 ላይ እንደተመዘገበው ኢየሱስ ምን ነገር አስገንዝቧል?
9 አስቀድሞ የተነገረው የመንግሥቱ የስብከት ሥራም ሆነ የኢየሱስ መገኘት ምልክት የሆኑት ሌሎች ገጽታዎች በአሁኑ ጊዜ ፍጻሜያቸውን እያገኙ ነው። በመሆኑም የዚህ ክፉ የነገሮች ሥርዓት ፍጻሜ ቀርቧል። ኢየሱስ “ስለዚያች ቀንና ስለዚያች ሰዓት ግን ከአባት ብቻ በቀር የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን የሚያውቅ የለም” ሲል መናገሩ እውነት ነው። (ማቴዎስ 24:4-14, 36) ይሁን እንጂ ኢየሱስ የተናገረው ትንቢት ‘ያችን ቀንና ሰዓት’ ዝግጁ ሆነን እንድንጠብቅ ይረዳናል።
-
-
ለይሖዋ ቀን ተዘጋጅታችኋል?መጠበቂያ ግንብ—1997 | መጋቢት 1
-
-
14. ይሖዋ በመጨረሻ ለኖኅ ምን ነግሮታል? ለምንስ?
14 የመርከቡ ሥራ ወደ መጠናቀቁ ሲቃረብ ኖኅ የጥፋት ውኃው መቼ እንደሚመጣ በትክክል ባያውቅም እንኳ የመምጫው ጊዜ እንደተቃረበ ሳይሰማው አይቀርም። በመጨረሻ ይሖዋ “ከሰባት ቀን በኋላ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት በምድር ላይ ዝናብ አዘንባለሁ” ሲል ነገረው። (ዘፍጥረት 7:4) ይህም ኖኅና ቤተሰቡ እንስሳትን ወደ መርከቡ ለማስገባትና እነርሱም ጭምር የጥፋት ውኃው ከመጀመሩ በፊት ለመግባት በቂ ጊዜ እንዲያገኙ አስችሏቸዋል። የዚህ ሥርዓት ጥፋት የሚጀምርበትን ቀንና ሰዓት ማወቅ አያስፈልገንም። የእንስሳትን ሕይወት የማዳን ሥራ አልተሰጠንም፤ ከጥፋቱ ለመትረፍ የተዘጋጁ ሰዎች ወደ ምሳሌያዊው መርከብ ማለትም ወደ አምላክ ሕዝቦች መንፈሳዊ ገነት በመግባት ላይ ናቸው።
-