-
ኢየሱስ የተናገረው ስለ ገሃነመ እሳት ነበር?መጠበቂያ ግንብ—2008 | ሰኔ 15
-
-
በገሃነመ እሳት መሠረተ ትምህርት የሚያምኑ አንዳንድ ሰዎች በማርቆስ 9:48 (ወይም ቁጥር 44 እና 46) ላይ የሚገኘውን የኢየሱስ አባባል ይጠቅሳሉ። ኢየሱስ በዚህ ጥቅስ ላይ ስለማይሞት ትልና ስለማይጠፋ እሳት ተናግሮ ነበር። አንድ ሰው ይህ ጥቅስ ምን ትርጉም እንዳለው ቢጠይቅህ ምን ብለህ ትመልሳለህ?
ግለሰቡ በሚጠቀምበት መጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ቁጥር 44ን, 46ን ወይም 48ን ሊያነብልህ ይችላል፤ በአንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ላይ እነዚህ ጥቅሶች ተመሳሳይ ሐሳቦች ይዘዋል።a የአዲስ ዓለም ትርጉም እንዲህ ይላል:- “ዓይንህም ቢያሰናክልህ አውጥተህ ጣለው፤ ሁለት ዓይን ኖሮህ ወደ ገሃነም ከምትጣል አንድ ዓይን ኖሮህ ወደ አምላክ መንግሥት ብትገባ ይሻልሃል፤ በገሃነም ትላቸው አይሞትም፤ እሳቱም አይጠፋም።”—ማር. 9:47, 48
-
-
ኢየሱስ የተናገረው ስለ ገሃነመ እሳት ነበር?መጠበቂያ ግንብ—2008 | ሰኔ 15
-
-
a አስተማማኝ በሆኑት ጥንታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ቅጂዎች ላይ ቁጥር 44 እና 46 አይገኙም። ምሑራን፣ ሁለቱ ቁጥሮች ከጊዜ በኋላ የተጨመሩ ሊሆኑ እንደሚችሉ ይገልጻሉ። ፕሮፌሰር አርኪባልድ ቶማስ ሮበርትሰን እንዲህ ሲሉ ጽፈዋል:- “ጥንታዊ በሆኑትና ከሁሉ በተሻሉት ቅጂዎች ላይ እነዚህ ሁለት ቁጥሮች አይገኙም። እነዚህ ቁጥሮች የተጨመሩት ከምዕራብና ከሶርያ (ባይዛንታይን) የጥንታዊ ጽሑፎች ቅጂዎች ነው። በቁጥር 48 ላይ ያለውን ሐሳብ የሚደግሙ ናቸው። በመሆኑም ቁጥር 44 እና 46 ትክክለኛ ባለመሆናቸው [አውጥተናቸዋል]።”
-