-
ክርስቲያን ሴቶች ከፍተኛ ግምትና አክብሮት ሊሰጣቸው ይገባልመጠበቂያ ግንብ—1995 | ሐምሌ 15
-
-
10 ፍቺን በተመለከተ ኢየሱስ “ሰው በሆነው ምክንያት ሁሉ ሚስቱን ሊፈታ ተፈቅዶለታልን?” የሚል ጥያቄ ተጠይቆ ነበር። በማርቆስ ዘገባ መሠረት ኢየሱስ “[ያለ ዝሙት ምክንያት] ሚስቱን ፈትቶ ሌላ የሚያገባ ሁሉ በእርሷ ላይ ያመነዝራል፤ እርስዋም ባልዋን ፈትታ ሌላ ብታገባ ታመነዝራለች” አላቸው። (ማርቆስ 10:10–12፤ ማቴዎስ 19:3, 9) እነዚህ በቀላል አነጋገር የተገለጹ ቃላት ለሴቶች አክብሮትን ያሳያሉ። እንዴት?
-
-
ክርስቲያን ሴቶች ከፍተኛ ግምትና አክብሮት ሊሰጣቸው ይገባልመጠበቂያ ግንብ—1995 | ሐምሌ 15
-
-
13. ኢየሱስ በክርስትና ሥርዓት ፍቺን በተመለከተ ለወንዶችም ሆነ ለሴቶች ያለው የአቋም መመዘኛ አንድ እንደሆነ ያሳየው እንዴት ነው?
13 በሦስተኛ ደረጃ “ባልዋን ፈትታ” በሚለው ሐረግ ኢየሱስ አንዲት ሴት ታማኝ ያልሆነ ባልዋን ለመፍታት ላላት መብት እውቅና ሰጥቷል፤ ይህ ዓይነቱ ድርጊት ቢኖርም በዘመኑ በነበረው የአይሁድ ሕግ ውስጥ አልተካተተም ነበር።c “አንዲት ሴት በፈቃድዋም ሆነ ያለ ፈቃድዋ ልትፈታ ብትችልም ወንድን መፍታት የሚቻለው ከፈለገ ብቻ ነው” ይባል ነበር። ሆኖም ኢየሱስ እንደተናገረው በክርስትና ሥርዓት ለወንድም ሆነ ለሴት የሚሠራው የአቋም መመዘኛ አንድ ነው።
-