-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 13—1 ዜና መዋዕል“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 7
-
-
23 የአንደኛ ዜና መጽሐፍ ለመጀመሪያው መቶ ዘመን ክርስቲያኖችም ትልቅ ጥቅም ነበረው። ማቴዎስና ሉቃስ ከዘር ሐረጉ ዝርዝር በመጥቀስ ኢየሱስ ክርስቶስ “የዳዊት ልጅ” እና ትክክለኛ መብት ያለው መሲሕ መሆኑን በግልጽ ማስቀመጥ ችለዋል። (ማቴዎስ 1:1–16፤ ሉቃስ 3:23-38) እስጢፋኖስ የመጨረሻ ምሥክርነቱን ሲደመድም ዳዊት የይሖዋን ቤት ለመገንባት ስላቀረበው ጥያቄና ሰሎሞን ግንባታውን ስለማከናወኑ ጠቅሷል። ከዚያም ‘ልዑሉ የሰው እጆች በሠሩት ቤት እንደማይኖር’ በመግለጽ በሰሎሞን ዘመን የተሠራው ቤተ መቅደስ የበለጠ ክብር ያለውን ሰማያዊ ነገር እንደሚያመለክት ጠቁሟል።—ሥራ 7:45-50
-
-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 27—ዳንኤል“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 15
-
-
21 ዳንኤል ስለ ‘ሰባ ሱባዔ’ የተናገረው ትንቢትም አለ። በትንቢቱ መሠረት ከ69 ሱባዔ ወይም ሳምንታት በኋላ “ገዥው መሲሕ” ይገለጣል። ኢየሩሳሌምን ለመጠገን “ዐዋጁ ከወጣ” ከ483 ዓመታት (69 ሲባዛ 7 ዓመታት) በኋላ የናዝሬቱ ኢየሱስ በዮርዳኖስ ወንዝ ውስጥ ተጠምቆ በመንፈስ ቅዱስ በመቀባት ክርስቶስ ወይም መሲሕ (የተቀባ ማለት ነው) ሆነ። ንጉሥ አርጤክስስ ኢየሩሳሌም እንድትጠገን አዋጅ ያስነገረው በ20ኛው የግዛት ዘመኑ ሲሆን ነህምያም አዋጁን ተግባራዊ አድርጎታል።g ኢየሱስ መሲሕ ሆኖ የተገለጠው በ29 ከክርስቶስ ልደት በኋላ ነበር። ከዚያ በኋላ ዳንኤል አስቀድሞ በትንቢት እንደተናገረው ኢየሩሳሌም በ70 ከክርስቶስ ልደት በኋላ ስትደመሰስ “ፍጻሜ” (የ1954 ትርጉም) ሆኗል።—ዳን. 9:24-27፤ ሉቃስ 3:21-23፤ 21:20
-