-
‘ፍትሕን በማድረግ’ ከአምላክ ጋር መሄድወደ ይሖዋ ቅረብ
-
-
13 የአምላክ ፍትሕ ምሕረት የሚንጸባረቅበት እንደሆነ ከተገነዘብን በረባ ባልረባው ሰውን ለመተቸት ወይም በማይመለከቱን ጉዳዮች ገብተን በሌሎች ላይ ለመፍረድ አንቸኩልም። ኢየሱስ በተራራ ስብከቱ ላይ “እንዳይፈረድባችሁ በሌሎች ላይ መፍረዳችሁን ተዉ” ሲል አስጠንቅቋል። (ማቴዎስ 7:1 የግርጌ ማስታወሻ) ሉቃስ እንደዘገበው ደግሞ ኢየሱስ “ሌሎችን አትኮንኑ፤ እናንተም ፈጽሞ አትኮነኑም” ሲል አክሎ ተናግሯል።a (ሉቃስ 6:37) ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መናገሩ ፍጽምና የጎደላቸው ሰዎች በሌሎች ላይ መፍረድ እንደሚቀናቸው መገንዘቡን ያሳያል። የኢየሱስ አድማጮች በሌሎች ላይ የመፍረድ ልማድ ከነበራቸው ይህን ልማዳቸውን እርግፍ አድርገው መተው ይጠበቅባቸው ነበር።
ምሥራቹን ሳናዳላ ለሁሉም ሰዎች በመስበክ መለኮታዊውን ፍትሕ እናንጸባርቃለን
14. በሌሎች ላይ ‘መፍረዳችንን መተው’ ያለብን ለምንድን ነው?
14 በሌሎች ላይ ‘መፍረዳችንን መተው’ ያለብን ለምንድን ነው? በመጀመሪያ ደረጃ እኛ እንዲህ የማድረግ ሥልጣን የለንም። ደቀ መዝሙሩ ያዕቆብ “ሕግ የሚሰጥና የሚፈርድ አንድ [ይሖዋ] ብቻ ነው” ሲል ማሳሰቢያ ሰጥቷል። በመሆኑም “በባልንጀራህ ላይ የምትፈርድ አንተ ማን ነህ?” የሚል ቀጥተኛ ጥያቄ አቅርቧል። (ያዕቆብ 4:12፤ ሮም 14:1-4) በተጨማሪም በወረስነው ኃጢአት ሳቢያ የተዛባ ፍርድ ወደ መስጠት ልናደላ እንችላለን። መሠረተ ቢስ ጥላቻ፣ ቅናት፣ ራስን ከፍ አድርጎ መመልከትና እነዚህን የመሳሰሉ ዝንባሌዎች ለሌሎች ሰዎች ያለንን አመለካከት ሊያዛቡብን ይችላሉ። ሌሎች ጉድለቶችም እንዳሉብን ማሰባችን የሰዎችን ስህተት ከመለቃቀም እንድንታቀብ ሊያደርገን ይገባል። የሰዎችን ልብ ማንበብም ሆነ ያሉበትን ሁኔታ ሙሉ በሙሉ መረዳት አንችልም። እንግዲያው የእምነት አጋሮቻችን የሚያደርጉትን ነገር በመጥፎ የምንተረጉም ወይም አምላክን ለማገልገል የሚያደርጉትን ጥረት የምንተች እኛ ማን ነን? የወንድሞቻችንንና የእህቶቻችንን ጉድለት ሳይሆን መልካም ጎናቸውን በመመልከት ይሖዋን ለመኮረጅ ጥረት ማድረጋችን ምንኛ የተሻለ ነው!
15. በአምላክ ሕዝቦች መካከል ምን ነገሮች ቦታ የላቸውም? ለምንስ?
15 የቤተሰባችንን አባላት ስለምንይዝበት መንገድስ ምን ማለት ይቻላል? በዛሬው ጊዜ፣ ቤት ሰላም የሰፈነበት ሊሆን ሲገባው አንዳንዴ ከሁሉ የከፋ ትችትና ነቀፋ የሚሰነዘርበት ቦታ መሆኑ ያሳዝናል። በቤተሰባቸው አባላት ላይ የስድብ ወይም የዱላ ናዳ የሚያወርዱ ባሎች፣ ሚስቶች ወይም ወላጆች ማየት የተለመደ ነው። ሆኖም ስድብ፣ አሽሙር እንዲሁም ሌላ ማንኛውም ዓይነት ጥቃት በይሖዋ ሕዝቦች መካከል ቦታ የላቸውም። (ኤፌሶን 4:29, 31፤ 5:33፤ 6:4) ኢየሱስ “መፍረዳችሁን ተዉ” እና “አትኮንኑ” ሲል የሰጠው ምክር በቤተሰብ ውስጥም እንደሚሠራ መዘንጋት አይኖርብንም። ፍትሕን ማንጸባረቅ ይሖዋ እኛን በሚይዘን መንገድ ሌሎችን መያዝንም እንደሚጨምር አስታውስ። ይሖዋ ጨካኝና ምሕረት የለሽ አምላክ አይደለም። ከዚህ ይልቅ ለሚወዱት ሰዎች “ከአንጀት የሚራራ” አምላክ ነው። (ያዕቆብ 5:11 የግርጌ ማስታወሻ) ልንኮርጀው የሚገባ ግሩም ምሳሌያችን ነው!
-
-
‘ፍትሕን በማድረግ’ ከአምላክ ጋር መሄድወደ ይሖዋ ቅረብ
-
-
a በበኩረ ጽሑፉ ላይ የሚገኘው አገላለጽ በሂደት ላይ ያለንና መቆም ያለበትን ድርጊት የሚያመለክት ነው። በመሆኑም ኢየሱስ አድማጮቹ እያደረጉ ያሉትን ነገር እንዲተዉ ይኸውም በሌሎች ላይ መፍረዳቸውን ወይም ሌሎችን መኮነናቸውን እንዲያቆሙ መምከሩ ነበር።
-