-
አንድ ሳምራዊ መልካም ባልንጀራ ሆኖ ተገኘመጠበቂያ ግንብ—1998 | ሐምሌ 1
-
-
የይሖዋን ፈቃድ ፈጽመዋል
አንድ ሳምራዊ መልካም ባልንጀራ ሆኖ ተገኘ
በኢየሱስ ዘመን በአይሁዳውያንና በአሕዛብ መካከል ግልጽ ጥላቻ ነበር። እንዲያውም ከጊዜ በኋላ የአይሁዳውያን ሚሽና እስራኤላውያን ሴቶች አይሁዳዊ ያልሆኑ ሴቶችን በአዋላጅነት እንዳይረዱ የሚከለክል ሕግ አውጥቶ ነበር፤ ምክንያቱም እንዲህ ማድረግ ሌላ ተጨማሪ አሕዛብ ወደ ዓለም እንዲመጣ መርዳት ስለሚሆን ነው።—አቦዳህ ዛራህ 2:1
ከአሕዛብ ይልቅ ሳምራውያን በሃይማኖትም ሆነ በዘር ከአይሁዳውያን ጋር ይበልጥ ይዛመዱ ነበር። ሆኖም እነሱም ጭምር እንደ ባዕድ ይቆጠሩ ነበር። ሐዋርያው ዮሐንስ “አይሁድ ከሳምራውያን ጋር አይተባበሩም” ሲል ጽፏል። (ዮሐንስ 4:9) ታልሙድ “አንድ ሳምራዊ ለአንድ አይሁዳዊ የሚሰጠው ቁራሽ ዳቦ ከአሳማ ሥጋ ይበልጥ የረከሰ ነው” ሲል ያስተምራል። እንዲያውም አንዳንድ አይሁዳውያን “ሳምራዊ” የሚለውን ቃል ለማላገጫና ለማዋረጃ ይጠቀሙበት ነበር።—ዮሐንስ 8:48
-
-
አንድ ሳምራዊ መልካም ባልንጀራ ሆኖ ተገኘመጠበቂያ ግንብ—1998 | ሐምሌ 1
-
-
ኢየሱስ ምሳሌውን በመቀጠል “አንድ ሳምራዊ ግን ሲሄድ ወደ እርሱ መጣ” አለ። ስለ አንድ ሳምራዊ መጠቀሱ የሕግ አዋቂው ጉጉት እንዲጨምር ሳያደርግ እንደማይቀር እሙን ነው። ኢየሱስ ስለዚህ ዘር ተስፋፍቶ የነበረውን አሉታዊ አመለካከት መደገፉን ይገልጽ ይሆን? ከዚህ በተቃራኒ ሳምራዊው አደጋ የደረሰበትን መንገደኛ ሲመለከት “አዘነለት።” ኢየሱስ እንዲህ አለ:- “ቀርቦም ዘይትና የወይን ጠጅ በቊስሎቹ ላይ አፍስሶ አሰራቸው፣ በራሱ አህያም ላይ አስቀምጦት ወደ እንግዶች ማደርያ ወሰደው ጠበቀውም።b በማግሥቱም ሁለት ዲናር አውጥቶ ለባለቤቱ ሰጠና:- ጠብቀው፣ ከዚህም በላይ የምትከስረውን ሁሉ እኔ ስመለስ እከፍልሃለሁ አለው።”—ሉቃስ 10:33-35
-