-
ክርስቲያን ሴቶች ከፍተኛ ግምትና አክብሮት ሊሰጣቸው ይገባልመጠበቂያ ግንብ—1995 | ሐምሌ 15
-
-
1, 2. (ሀ) ኢየሱስ ከሳምራዊቷ ሴት ጋር በውኃ ጉድጓድ አጠገብ ያደረገው ውይይት ምን ትኩረት የሚስብ ጉዳይ ፈጠረ? ለምንስ? (የግርጌ ማስታወሻውንም ተመልከት።) (ለ) ኢየሱስ ለሳምራዊቷ ሴት በመስበክ በተግባር ያሳየው ምንድን ነው?
ኢየሱስ በ30 እዘአ መገባደጃ ሲካር በምትባል ከተማ አቅራቢያ በሚገኝ የጥንት የውኃ ጉድጓድ አጠገብ አንድ ቀትር ላይ ኢየሱስ ሴቶች እንዴት መያዝ እንዳለባቸው የነበረውን ስሜት አሳይቷል። ከጠዋት ጀምሮ በሰማሪያ ኮረብታማ ስፍራዎች ሲጓዝ ስለዋለ በጣም ተዳክሞ፣ ተርቦና ተጠምቶ ይህ ጉድጓድ ወዳለበት ሥፍራ ደረሰ። በውኃው ጉድጓድ አጠገብ እንደ ተቀመጠ አንዲት ሳምራዊት ሴት ውኃ ልትቀዳ መጣች። ኢየሱስ “ውኃ አጠጪኝ” በማለት ጠየቃት። ሴትየዋ በመገረም ትክ ብላ ሳትመለከተው አልቀረችም። “አንተ የይሁዳ ሰው ስትሆን ሳምራዊት ሴት ከምሆን ከእኔ መጠጥ እንዴት ትለምናለህ?” በማለት ጠየቀችው። ደቀ መዛሙርቱ ምግብ ገዝተው ሲመለሱ ኢየሱስ “ከሴት ጋር በመነጋገሩ” ተደነቁ።—ዮሐንስ 4:4–9, 27
2 ይህቺ ሴት ጥያቄ እንድትጠይቅ ያነሣሣትና ደቀ መዛሙርቱ ለሁኔታው ይህን ያህል ትኩረት እንዲሰጡት ያደረጋቸው ምንድን ነው? ሴትየዋ ሳምራዊት ነበረች፤ አይሁዶች ደግሞ ከሳምራውያን ጋር ምንም ግንኙነት አልነበራቸውም። (ዮሐንስ 8:48) ይሁን እንጂ ሁኔታው ይህን ያህል ትኩረት እንዲሰጠው ያደረገ ሌላም ምክንያት እንደ ነበረ ግልጽ ነው። በዚያ ወቅት የነበረው የረቢዎች ወግ ከሴት ጋር በአደባባይ መነጋገርን ያወግዝ ነበር።a ሆኖም ኢየሱስ ለዚህች ቅን ሴት በአደባባይ ሰብኮላታል፤ እንዲያውም መሲሕ መሆኑን ገልጾላታል። (ዮሐንስ 4:25, 26) ስለዚህ ኢየሱስ ሴቶችን ዝቅ የሚያደርጉትን ቅዱስ ጽሑፋዊ ያልሆኑ ወጎች ጨምሮ በማናቸውም ወግ እንደማይመራ አሳይቷል። (ማርቆስ 7:9–13) ከዚህ ይልቅ ኢየሱስ ባደረገው ነገርና ባስተማረው ትምህርት ሴቶች በክብር መያዝ እንዳለባቸው ጠቁሟል።
-
-
ክርስቲያን ሴቶች ከፍተኛ ግምትና አክብሮት ሊሰጣቸው ይገባልመጠበቂያ ግንብ—1995 | ሐምሌ 15
-
-
a ዘ ኢንተርናሽናል ስታንደርድ ባይብል ኢንሳይክሎፔድያ እንዲህ በማለት ይገልጻል፦ “ሴቶች ከወንዶች እንግዶች ጋር ምግብ አይበሉም ነበር፤ ወንዶች ከሴቶች ጋር መነጋገር የለባቸውም ይባል ነበር። . . . በተለይ በአደባባይ ከሴት ጋር መነጋገር ነውር ነበር።” የረቢዎችን ትምህርቶች የያዘው የአይሁዶች ሚሽና እንዲህ በማለት ይመክራል፦ “ከሴት ጋር ብዙ አታውራ። . . . ከሴት ጋር ብዙ የሚያወራ ሰው በራሱ ላይ ጉዳት ያመጣል፣ የሕጉን ጥናት ችላ ይላል በመጨረሻም ገሃነም ይገባል።”—አቦት 1:5
-