የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “የመንፈስ ፍሬ” አምላክን ያስከብራል
    መጠበቂያ ግንብ—2011 | ሚያዝያ 15
    • 3. (ሀ) “የመንፈስ ፍሬ” ማፍራታችን አምላክን የሚያስከብረው እንዴት ነው? (ለ) የትኞቹን ጥያቄዎች እንመረምራለን?

      3 መንፈስ ቅዱስ የሚያፈራቸው ባሕርያት የዚህ መንፈስ ምንጭ የሆነውን የይሖዋ አምላክን ማንነት የሚያንጸባርቁ ናቸው። (ቆላ. 3:9, 10) ኢየሱስ ለተከታዮቹ “ብዙ ፍሬ ማፍራታችሁን ብትቀጥሉ . . . በዚህ አባቴ ይከበራል” ብሎ በነገራቸው ጊዜ ክርስቲያኖች አምላክን ለመምሰል እንዲጥሩ የሚያነሳሳቸው ዋነኛው ምክንያት ምን እንደሆነ ጠቁሟል።a (ዮሐ. 15:8) “የመንፈስ ፍሬ” እያፈራን ስንሄድ ውጤቱ በአነጋገራችንና በድርጊታችን በግልጽ ይታያል፤ ይህ ደግሞ ለአምላካችን ውዳሴ ያመጣለታል። (ማቴ. 5:16) የመንፈስ ፍሬ፣ የሰይጣን ዓለም ከሚያፈራቸው ባሕርያት የተለየ የሆነው በምን መንገዶች ነው? የመንፈስ ፍሬን ማፍራት የምንችለው እንዴት ነው? እንዲህ ማድረግ አስቸጋሪ የሚሆንብን ለምን ሊሆን ይችላል? ስለ መጀመሪያዎቹ ሦስት የመንፈስ ፍሬ ገጽታዎች ይኸውም ስለ ፍቅር፣ ደስታና ሰላም እየተወያየን ስንሄድ እነዚህን ጥያቄዎች እንመረምራለን።

  • “የመንፈስ ፍሬ” አምላክን ያስከብራል
    መጠበቂያ ግንብ—2011 | ሚያዝያ 15
    • a ኢየሱስ እዚህ ላይ የጠቀሰው ፍሬ ‘የመንፈስ ፍሬን’ እንዲሁም ክርስቲያኖች በመንግሥቱ የስብከት ሥራ አማካኝነት ለአምላክ የሚያቀርቡትን “የከንፈር ፍሬ” ይጨምራል።—ዕብ. 13:15

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ