የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዳግመኛ መወለድ ምን ያህል አስፈላጊ ነው?
    መጠበቂያ ግንብ—2009 | ሚያዝያ 1
    • ኢየሱስ ከኒቆዲሞስ ጋር ባደረገው ውይይት ላይ ዳግመኛ መወለድ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ የገለጸበትን መንገድ ልብ በል። “ማንም ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የአምላክን መንግሥት ሊያይ አይችልም” ብሏል። (ዮሐንስ 3:3) “በቀር” እና “አይችልም” የሚሉት ቃላት እንደ አዲስ መወለድ ምን ያህል አስፈላጊ መሆኑን የሚያጎሉ ናቸው። ይህን በምሳሌ ለማስረዳት ያህል፣ አንድ ሰው “ፀሐይ ካልወጣች በቀር ብርሃን ሊኖር አይችልም” ቢል ብርሃን እንዲኖር ፀሐይ መውጣቷ የግድ አስፈላጊ መሆኑን መግለጹ ነው። በተመሳሳይም ኢየሱስ የአምላክን መንግሥት ለማየት ዳግመኛ መወለድ የግድ አስፈላጊ መሆኑን መናገሩ ነበር።

  • ዳግመኛ መወለድ በእኛ ምርጫ ላይ የተመካ ነው?
    መጠበቂያ ግንብ—2009 | ሚያዝያ 1
    • ኢየሱስ የተናገረውን ሐሳብ ልብ ብለን ካነበብን ዳግመኛ መወለድ፣ በግለሰቦች ምርጫ ላይ የተመካ መሆኑን እንዳላስተማረ መገንዘብ እንችላለን። እንዲህ የምንለው ለምንድን ነው? “ዳግመኛ መወለድ” ተብሎ የተተረጎመው የግሪክኛ ሐረግ “ከላይ መወለድ” ተብሎም ሊተረጎም ይችላል።a በዚህ አተረጓጎም መሠረት አንድ ሰው እንደ አዲስ መወለድን ማግኘት የሚችለው “ከላይ” ማለትም በሰማይ ከሚኖረው “አባት” ነው። (ዮሐንስ 19:11፤ ያዕቆብ 1:17) አዎን፣ አንድ ሰው ዳግመኛ እንዲወለድ የሚያደርገው አምላክ ነው።—1 ዮሐንስ 3:9

  • ዳግመኛ መወለድ በእኛ ምርጫ ላይ የተመካ ነው?
    መጠበቂያ ግንብ—2009 | ሚያዝያ 1
    • a በርካታ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ዮሐንስ 3:3⁠ን በዚህ መንገድ ተርጉመውታል። ለምሳሌ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጽሑፍ ጋር ይህን ጥቅስ እንደሚከተለው በማለት አስቀምጦታል፦ “ማንም ዳግመኛ ካልተወለደ [‘ከላይ ካልተወለደ፣’ የግርጌ ማስታወሻ] በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም።”

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ