-
‘ሁሉንም ነገር አዲስ የሚያደርገው’ ይሖዋ—ለማደስ የሚጠቀምበት ኃይልወደ ይሖዋ ቅረብ
-
-
3. በሐዋርያት ሥራ 3:21 ላይ ምን የሚያጽናና ተስፋ ተገልጿል? ይሖዋ ይህን ተስፋ የሚፈጽመውስ በምን አማካኝነት ነው?
3 በመሆኑም ይሖዋ አንድን ነገር ለማደስ ወይም ቀድሞ ወደነበረበት ሁኔታ ለመመለስ የሚያስችል ኃይል እንዳለው ማወቃችን ምንኛ የሚያጽናና ነው! ቀጥለን እንደምንመለከተው አምላክ በምድር ላሉት ልጆቹ በርካታ ነገሮችን መልሶ ይሰጣቸዋል። እንዲያውም መጽሐፍ ቅዱስ ይሖዋ “ነገሮች ሁሉ የሚታደሱበት ዘመን” ለማምጣት ዓላማ እንዳለው ይገልጻል። (የሐዋርያት ሥራ 3:21) ይህን የሚያከናውነው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በሚመራው መሲሐዊ መንግሥት አማካኝነት ነው። ማስረጃዎቹ እንደሚያሳዩት ይህ መንግሥት በ1914 በሰማይ መግዛት ጀምሯል።a (ማቴዎስ 24:3-14) ይሁንና የሚታደሰው ነገር ምንድን ነው? ይሖዋ ከሚያከናውናቸው ታላላቅ የተሃድሶ ሥራዎች መካከል አንዳንዶቹን እስቲ እንመልከት። ከእነዚህ የተሃድሶ ሥራዎች መካከል አንዱ በአሁኑ ጊዜ በመፈጸም ላይ ሲሆን ሌሎቹ ደግሞ ወደፊት በስፋት ይከናወናሉ።
-
-
‘ሁሉንም ነገር አዲስ የሚያደርገው’ ይሖዋ—ለማደስ የሚጠቀምበት ኃይልወደ ይሖዋ ቅረብ
-
-
a “ነገሮች ሁሉ የሚታደሱበት ዘመን” የጀመረው መሲሐዊው መንግሥት ተቋቁሞ የታማኙ ንጉሥ የዳዊት ወራሽ ዙፋን ላይ በተቀመጠበት ጊዜ ነው። ይሖዋ ለዳዊት፣ ዘሩ ለዘላለም እንደሚገዛ ቃል ገብቶለት ነበር። (መዝሙር 89:35-37) ይሁን እንጂ ኢየሩሳሌም በ607 ዓ.ዓ. በባቢሎን ከጠፋች በኋላ በአምላክ ዙፋን ላይ የነገሠ የዳዊት ዘር አልነበረም። ሆኖም የዳዊት ዘር ሆኖ በምድር ላይ የተወለደው ኢየሱስ በሰማይ ንጉሥ ሆኖ ሲሾም አስቀድሞ በትንቢት የተነገረለት የዙፋን ወራሽ ሆኗል።
-