የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • መጽሐፍ ቅዱስ የአምላክ ቃል ነው
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 6. ሁሉም ሰው ሊያገኘው የሚችል መጽሐፍ

      በታሪክ ውስጥ የመጽሐፍ ቅዱስን ያህል በስፋት የተተረጎመና የተሰራጨ መጽሐፍ የለም። የሐዋርያት ሥራ 10:34, 35⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      • አምላክ ቃሉ ይህን ያህል በስፋት እንዲተረጎምና እንዲሰራጭ የሚፈልገው ለምንድን ነው?

      • ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ካነሳናቸው ነጥቦች መካከል ትኩረትህን የሳበው የትኛው ነው?

      የተለያየ ዘርና የቆዳ ቀለም ያላቸው ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስን በራሳቸው ቋንቋ ሲያነብቡ

      ወደ

      100%

      የሚጠጋ የዓለማችን ሕዝብ

      መጽሐፍ ቅዱስን ሊገባው በሚችለው ቋንቋ ማግኘት ይችላል

      ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል

      ከ3,000

      በሚበልጡ ቋንቋዎች

      ይገኛል

      ከ5,000,000,000

      በላይ ቅጂዎች እንደታተሙ ይታመናል

      በሕትመት ብዛት የትኛውም መጽሐፍ አይወዳደረውም

  • የይሖዋ ወዳጅ መሆን ትችላለህ
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 3. የይሖዋ ወዳጅ ለመሆን ምን ማድረግ ያስፈልጋል?

      ይሖዋ ሁሉንም ሰዎች ይወዳል፤ ‘የጠበቀ ወዳጅነት ያለው ግን ከቅኖች ጋር ነው።’ (ምሳሌ 3:32) ይሖዋ ወዳጆቹ በእሱ ፊት ጥሩ የሆኑትን ነገሮች እንዲያደርጉና በእሱ ፊት መጥፎ ከሆኑ ነገሮች እንዲርቁ ይፈልጋል። አንዳንዶች ይሖዋ ጥሩና መጥፎ የሆነውን ነገር በተመለከተ ያወጣውን መሥፈርት ፈጽሞ ሊያሟሉ እንደማይችሉ ይሰማቸው ይሆናል። ሆኖም ይሖዋ ያለብንን የአቅም ገደብ ይረዳል። ከልባችን እስከወደድነውና እሱን ለማስደሰት የምንችለውን ሁሉ እስካደረግን ድረስ ይቀበለናል።—መዝሙር 147:11፤ የሐዋርያት ሥራ 10:34, 35

  • ለጉባኤው አንድነት የበኩልህን አስተዋጽኦ አበርክት
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 4. ጭፍን ጥላቻን አስወግድ

      ሁሉንም ወንድሞቻችንን መውደድ እንዳለብን እናውቃለን። ሆኖም ከእኛ የተለየ ዘር ወይም ባሕል ያላቸውን ሰዎች መውደድ ከባድ ሊሆንብን ይችላል። በዚህ ረገድ ምን ይረዳናል? የሐዋርያት ሥራ 10:34, 35⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      • ይሖዋ ሁሉንም ዓይነት ሰዎች ምሥክሮቹ አድርጎ ይቀበላል። ይህን ማወቅህ ከአንተ የተለየ ዘር ወይም ባሕል ላላቸው ሰዎች ባለህ አመለካከት ላይ ምን ለውጥ ሊያመጣ ይገባል?

      • በአካባቢህ የሚኖሩ በርካታ ሰዎች ምን ዓይነት ጭፍን ጥላቻ አላቸው? እንዲህ ያለውን ጭፍን ጥላቻ ማስወገድ ያለብህ ለምንድን ነው?

      ሁለተኛ ቆሮንቶስ 6:11-13⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      • ከአንተ የተለየ ባሕልና አስተዳደግ ካላቸው ሰዎች ጋር ለመቀራረብ ምን ይረዳሃል?

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ