-
“ወደ መቄዶንያ ተሻገር”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
16. ጳውሎስና ሲላስ በተገረፉ ማግስት ነገሩ የተገላቢጦሽ የሆነው እንዴት ነው?
16 ጳውሎስና ሲላስ በተገረፉ ማግስት የከተማዋ ሕግ አስከባሪዎች ሁለቱ ሰዎች እንዲፈቱ ትእዛዝ አስተላለፉ። ይሁን እንጂ ጳውሎስ እንዲህ አለ፦ “እኛ የሮም ዜጎች ሆነን ሳለ ያለፍርድ በሕዝብ ፊት ገርፈው እስር ቤት ወረወሩን። ታዲያ አሁን በድብቅ አስወጥተው ሊጥሉን ይፈልጋሉ? እንዲህማ አይሆንም! እነሱ ራሳቸው መጥተው ይዘውን ይውጡ።” የከተማዋ ሕግ አስከባሪዎች፣ ሁለቱ ሰዎች ሮማውያን መሆናቸውን ሲሰሙ “ፍርሃት አደረባቸው”፤ ምክንያቱም የሰዎቹን መብት ጥሰዋል።d አሁን ነገሩ የተገላቢጦሽ ሆነ። ደቀ መዛሙርቱ የተደበደቡት በሕዝብ ፊት ነበር፤ በመሆኑም ሕግ አስከባሪዎቹ በሕዝብ ፊት ይቅርታ መጠየቅ ይኖርባቸዋል። ከተማዋን ለቀው እንዲሄዱም ጳውሎስንና ሲላስን ለመኗቸው። ሁለቱ ደቀ መዛሙርት ይህን ለማድረግ ተስማሙ፤ ከከተማዋ ከመውጣታቸው በፊት ግን ጊዜ ወስደው አዳዲሶቹን ደቀ መዛሙርት አበረታቷቸው። ከተማዋን ለቀው የሄዱት ይህን ካደረጉ በኋላ ነው።
-
-
“ወደ መቄዶንያ ተሻገር”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
d በሮማውያን ሕግ መሠረት ዜጎች ምንጊዜም ጉዳያቸው በተገቢው መንገድ ችሎት ፊት ሊታይ ይገባል፤ እንዲሁም አንድ ሰው ጥፋተኛ እንደሆነ ሳይፈረድበት በሕዝብ ፊት አይቀጣም።
-