-
ተቃውሞ ቢኖርም “የይሖዋ ቃል . . . እየተስፋፋና እያሸነፈ ሄደ”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
15. መናፍስታዊ ድርጊትንና ከዚህ ልማድ ጋር ንክኪ ያላቸውን ነገሮች በተመለከተ የኤፌሶን ነዋሪዎች ምን ምሳሌ ትተውልናል?
15 በአስቄዋ ልጆች ላይ የደረሰው ውርደት ብዙዎች አምላክን እንዲፈሩ አደረገ፤ በዚህም የተነሳ መናፍስታዊ ድርጊታቸውን እርግፍ አድርገው በመተው አማኞች ሆኑ። በኤፌሶን አስማታዊ ድርጊቶች ተስፋፍተው ነበር። መተት መሥራትና ክታብ ማሰር የተለመዱ ነገሮች ነበሩ፤ ድግምትም እንዲሁ፤ ብዙ የድግምት መጻሕፍትም ነበሩ። በአምላክ ያመኑ ብዙ የኤፌሶን ነዋሪዎች ለአስማታዊ ድርጊቶች የሚጠቀሙባቸውን መጻሕፍት አምጥተው በሕዝብ ፊት አቃጠሉ፤ እነዚህ መጻሕፍት አሁን ባለው የዋጋ ተመን መሠረት በአሥር ሺዎች የሚቆጠር ዶላር ሳያወጡ አይቀሩም።d ሉቃስ “በዚህ መንገድ የይሖዋ ቃል በኃይል እየተስፋፋና እያሸነፈ ሄደ” በማለት ዘግቧል። (ሥራ 19:17-20) አዎ፣ እውነት በሐሰት ትምህርትና በአጋንንታዊ ድርጊት ላይ ታላቅ ድል ተቀዳጀ! እነዚያ ታማኝ ሰዎች ለእኛ ጥሩ ምሳሌ ይሆኑናል። እኛም የምንኖረው በመናፍስታዊ ድርጊት በተሞላ ዓለም ውስጥ ነው። ከመናፍስታዊ ድርጊት ጋር ንክኪ ያለው ነገር ካለን የኤፌሶን ነዋሪዎች እንዳደረጉት ወዲያውኑ ማስወገድ ይኖርብናል! ምንም ያህል ከፍተኛ ዋጋ የሚያስከፍለን ቢሆን እንዲህ ካለው አስጸያፊ ድርጊት መራቅ አለብን።
-
-
ተቃውሞ ቢኖርም “የይሖዋ ቃል . . . እየተስፋፋና እያሸነፈ ሄደ”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
d ሉቃስ እነዚህ መጻሕፍት 50,000 የብር ሳንቲሞች እንደሚያወጡ ጠቅሷል። እነዚህ የብር ሳንቲሞች ዲናር ከሆኑ ዋጋቸው በጣም ብዙ ነው፤ በዚያ ዘመን አንድ ሠራተኛ ይህን የሚያህል ገንዘብ ለማግኘት በሳምንት ሰባቱንም ቀን ቢሠራ እንኳ 50,000 ቀናት ማለትም 137 ዓመታት ገደማ ይፈጅበታል።
-