-
ክርስትያኖች በዘመን መለወጫ በዓል መካፈል ይኖርባቸዋልን?ንቁ!—2002 | ጥር 8
-
-
መጽሐፍ ቅዱስ “በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን” በማለት ክርስቲያኖችን አጥብቆ ይመክራቸዋል።a (ሮሜ 13:12-14፤ ገላትያ 5:19-21፤ 1 ጴጥሮስ 4:3) መጽሐፍ ቅዱስ የሚያወግዛቸው መረን የለቀቁ ተግባራት በዘመን መለወጫ በዓል ላይ ባብዛኛው ስለሚንጸባረቁ ክርስቲያኖች በዚህ በዓል አይካፈሉም። ይህ ማለት ግን ክርስቲያኖች ደስታ የራቃቸው ሰዎች ናቸው ማለት አይደለም። እንዲያውም የአምላክ አገልጋዮች ደስተኞች እንዲሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ደጋግሞ እንደሚናገር ያውቃሉ። ደግሞም ደስተኛ የሚሆኑበት ብዙ ምክንያት አላቸው። (ዘዳግም 26:10, 11፤ መዝሙር 32:11፤ ምሳሌ 5:15-19፤ መክብብ 3:22፤ 11:9) መጽሐፍ ቅዱስ በመብልና በመጠጥ ደስታ እንደሚገኝም ይናገራል።—መዝሙር 104:15፤ መክብብ 9:7ለ
-
-
ክርስትያኖች በዘመን መለወጫ በዓል መካፈል ይኖርባቸዋልን?ንቁ!—2002 | ጥር 8
-
-
a በአንደኛው መቶ ዘመን እነዚህ ተግባራት በሮም የተለመዱ ስለነበሩ ጳውሎስ ስለ ‘ፈንጠዝያና ስካር’ ያቀረበው ሐሳብ በዘመን መለወጫ በዓል ወቅት የሚደረጉትንም ሳይጨምር አይቀርም።
-