-
የጌታ ራት ስንት ጊዜ መከበር አለበት?መጠበቂያ ግንብ—1994 | መጋቢት 15
-
-
በተጨማሪም ኢየሱስ ይህን በዓል ካስጀመረ በኋላ በአይሁዳውያን አቆጣጠር መሠረት ኒሳን 14 ቀን እንደሞተ አስታውስ።a ይህ ቀን አይሁዳውያን በ16ኛው መቶ ዘመን ከዘአበ ከግብጻውያን እጅ ነፃ መውጣታቸውን የሚያስቡበት የማለፍ ቀን ነበር። በዚያ ጊዜ እስራኤላውያን አቅርበውት የነበረው የበግ መሥዋዕት የይሖዋ መልአክ የግብጽን በኩራት ሁሉ በሚመታበት ጊዜ የአይሁድ በኩራት ከመመታት እንዲድኑ አስችሏል።—ዘጸአት 12:21, 24–27
ይህ ስለነገሩ ያለንን ግንዛቤ የሚያዳብርልን እንዴት ነው? ክርስቲያኑ ሐዋርያ ጳውሎስ “ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአልና” ሲል ጽፏል። (1 ቆሮንቶስ 5:7) የኢየሱስ ሞት የሰው ልጆች ታላቅ ደህንነት እንዲያገኙ የሚያስችል ታላቅ የማለፍ መሥዋዕት ነው። ስለሆነም የክርስቶስ ሞት መታሰቢያ በዓል ለክርስቲያኖች የአይሁድ የማለፍ በዓል ምትክ ነው።—ዮሐንስ 3:16
የማለፍ በዓል ዓመታዊ በዓል ነበር። ስለዚህ የመታሰቢያውም በዓል በዓመት አንዴ ቢከበር ምክንያታዊ ነው። የማለፍ በዓል ማለትም ኢየሱስ የሞተበት ቀን ሁልጊዜ በአይሁዳውያን የኒሳን ወር በ14ኛው ቀን ላይ ይውላል። ስለዚህ የክርስቶስ ሞት በአይሁዳውያን አቆጣጠር መሠረት ኒሳን 14 በሚውልበት ቀን በዓመት አንድ ጊዜ መከበር ይኖርበታል። በ1994 ይህ ቀን የሚውለው ቅዳሜ መጋቢት 26 ፀሐይ ከጠለቀች በኋላ ይሆናል። ታዲያ የሕዝበ ክርስትና አብያተ ክርስቲያናት ይህን ቀን ልዩ በዓል አድርገው የማያከብሩት ለምንድን ነው? በአጭሩ ታሪክን መመርመር ለዚህ ጥያቄ መልስ ይሰጣል።
-
-
የጌታ ራት ስንት ጊዜ መከበር አለበት?መጠበቂያ ግንብ—1994 | መጋቢት 15
-
-
a የአይሁዶች የመጀመሪያ ወር የሆነው ኒሳን የሚጀምረው አዲስ ጨረቃ ከታየችበት ጊዜ ጀምሮ ነው። ስለዚህ ኒሳን 14 ሁልጊዜ የሚውለው ሙሉ ጨረቃ ላይ ነው።
-