-
ሥራችሁ እሳቱን ይቋቋም ይሆን?መጠበቂያ ግንብ—1998 | ኅዳር 1
-
-
13. በጳውሎስ ምሳሌ ውስጥ የተጠቀሰው እሳት ምን ያመለክታል? ሁሉም ክርስቲያኖች ንቁ መሆን ያለባቸውስ ለምን ነገር ነው?
13 ሁላችንም በሕይወታችን ውስጥ የሚያጋጥመን እሳት አለ። ይህም በእምነታችን ላይ የሚደርሱ ፈተናዎች ናቸው። (ዮሐንስ 15:20፤ ያዕቆብ 1:2, 3) የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች፣ እውነትን የሚያስተምሩት እያንዳንዱ ሰው ወደፊት እንደሚፈተን ማወቅ አስፈልጓቸው ነበር። እኛም ብንሆን ይህን ማወቅ አለብን። በጥሩ ሁኔታ የማናስተምር ከሆነ ውጤቱ አሳዛኝ ይሆናል። ጳውሎስ እንዲህ ሲል አስጠንቅቋል:- “ማንም በእርሱ ላይ ያነጸው ሥራ ቢጸናለት ደመወዙን ይቀበላል፤ የማንም ሥራ የተቃጠለበት ቢሆን ይጐዳበታል፣ እርሱ ራሱ ግን ይድናል ነገር ግን በእሳት እንደሚድን ይሆናል።”c—1 ቆሮንቶስ 3:14, 15
14. (ሀ) ክርስቲያን ደቀ መዛሙርት አድራጊዎች ‘ጉዳት ሊደርስባቸው’ የሚችለው እንዴት ሊሆን ይችላል? ሆኖም በእሳት ውስጥ እንዳለፉ ሆነው መዳንን ማግኘት የሚችሉት እንዴት ነው? (ለ) ሊገጥመን የሚችለውን ጉዳት መቀነስ የምንችለው እንዴት ነው?
14 በእርግጥም ሊጤን የሚገባው አነጋገር ነው! አንድ ሰው ደቀ መዝሙር እንዲሆን ለመርዳት ብዙ ከደከምን በኋላ ግለሰቡ በፈተና ወይም በስደት ሲሸነፍ ብሎም ከእውነት መንገድ ሲወጣ መመልከት እጅግ የሚያሳዝን ሊሆን ይችላል። ጳውሎስም ቢሆን እንዲህ ዓይነት ነገር መድረሱ ለገነባው ሰው ጉዳት መሆኑን ሲናገር ይህንኑ መግለጹ ነበር። ሁኔታው የሚያስከትልብን ሥቃይ ከፍተኛ ሊሆን ስለሚችል መዳናችን “በእሳት [“ውስጥ አልፎ፣” NW] እንደሚድን” ሰው ተደርጎ ተገልጿል። ይህም ንብረቱ ሁሉ ተቃጥሎበት ሕይወቱ ብቻ ከተረፈለት ሰው ጋር ሊመሳሰል ይችላል። እኛ በበኩላችን የዚህ ዓይነቱን አሳዛኝ ሁኔታ መከሰት መቀነስ የምንችለው እንዴት ነው? ጠንካራ በሆኑ ቁሳቁሶች በመገንባት ነው! ተማሪዎቻችንን ልባቸውን በሚነካ መንገድ ካስተማርናቸውና እንደ ጥበብ፣ ማስተዋል፣ ይሖዋን መፍራትና እውነተኛ እምነት ማሳየት የመሳሰሉ ውድ ክርስቲያናዊ ባሕርያትን ከፍ አድርገው እንዲመለከቱ የምናበረታታቸው ከሆነ ጠንካራ በሆኑና እሳትን መቋቋም በሚችሉ ቁሳቁሶች እየገነባን ነው ማለት ነው። (መዝሙር 19:9, 10፤ ምሳሌ 3:13–15፤ 1 ጴጥሮስ 1:6, 7) እነዚህን ባሕርያት ያዳበሩ ሰዎች የአምላክን ፈቃድ በማድረግ ይቀጥላሉ፤ እርግጠኛ የሆነው ለዘላለም ሕያው ሆኖ የመኖር ተስፋ የእነሱ ይሆናል። (1 ዮሐንስ 2:17) ሆኖም የጳውሎስን ምሳሌ ተግባራዊ ልናደርግ የምንችለው እንዴት ነው? አንዳንድ ምሳሌዎችን ተመልከቱ።
-
-
ሥራችሁ እሳቱን ይቋቋም ይሆን?መጠበቂያ ግንብ—1998 | ኅዳር 1
-
-
c ጳውሎስ የመዳኑ ሁኔታ አጠራጣሪ ነው ያለው የሚገነባውን ሰው ሳይሆን ‘ሥራውን’ ነው። ዘ ኒው ኢንግሊሽ ባይብል ጥቅሱን እንዲህ በማለት አስቀምጦታል:- “የአንድ ሰው ሕንፃ ጸንቶ ከቆመ፣ ሽልማት ያገኝበታል። ከተቃጠለበት ግን ኪሳራውን ሊሸከም ይገባዋል፤ ቢሆንም ከእሳት እንደሚድን ሰው ሕይወቱን ብቻ ሊያተርፍ ይችላል።”
-